እንደ መግቢያ
1975 ዓ.ም.፡፡ በመሀል ሀገር የነበረው የፖለቲካ ግለት ከብዙ ደም መፋሰስ በኋላ ወደ ጠረፍ እና የገጠር
ከተሞች አፈገፈገ፡፡ በ‹‹ምርጥ መኮንኖች›› የተመሰረተው መንግስትም አንፃራዊ ሰላም ያገኘ መሰለ፡፡ አስቀድሞ
‹‹ወታደራዊ ክንፍ›› አቋቁሞ የነበረው የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢህአፓ) በሀገሪቱ ዋና ዋና
ከተሞች ለማቀጣጠል ሞክሮት የነበረው አብዮት ከፍተኛ ዋጋ አስከፍሎት ከሸፈ፡፡ ለክፉ ቀን ‹‹አማራጬ››
ያለው ወታደራዊ ክንፉም ቢሆን ለሶስት በመከፈሉ በእጅጉ ተዳከመ (ትግል በቃን ብለው ወደ ምዕራብ ሀገራት
ለመሰደድ በወሰኑ፣ ኢህአፓን ይዘን እስከመጨረሻው እንፋለማለን ባሉና ‹‹ኢህአፓ ዴሞክራት አይደለም››
በሚል ተገንጥለው ‹‹ኢህዴን›› የተባለ አዲስ ድርጅት በመሰረቱ) ከዚህ በተቃራኒው በመገንጠል እና በብሄር
ጥያቄ ዙሪያ የተሰባሰቡት ሻዕቢያ፣ ህወሓት እና በሽብርተኝነት የተፈረጀው ኦነግ የተሻለ ድርጅታዊ አቅም
መፍጠር ቻሉ፡፡
…በሁለት ወጣት ታጋዮች የሚመራ ከህወሓት የጦር ሰፈር (ደደቢት) የተነሳ አንድ ልኡክ ከኢትዮጵያ መንግስት የመረጃ ሰራተኞች እናየገጠር ካድሬዎች አይን ተሸሽጎ በከፍተኛ ጥንቃቄ ጉዞ ጀምሯል፡፡ መድረሻ ነጥቡ ‹‹ደባዜን›› የተሰኘች ከተማ ነች፡፡ ልኡኩ ከብዙ ቀናትበኋላ የኦሮሚያ ገጠር ከተማ በሆነችው ደባዜን ደረሰ፡፡ በወቅቱ ደባዜን የኦሮሞ ነፃ አውጪ ግንባር /ኦነግ/ ወታደራዊ ቤዝ ስትሆን ትግረኛተናጋሪ ታጋዮቹ ወደ አካባቢው የመጡት በድርጅታቸው ህወሓት እና ኦነግ መካከል በተፈረመ ስምምነት መሰረት ነው፤ የስምምነቱ ይዘት‹‹የህወሓት ታጋዮች ለኦነግ ታጋዮች ወታደራዊ ስልጠና እንዲሰጡ፣ ካድሬዎችን እንዲያነቁ እና ሁለቱ ድርጅቶች በትጥቅ ትግሉም ሆነከትጥቅ ትግሉ በኋላ በጋራ እንዲሰሩ›› የሚል ነው፡፡ ሆኖም በሁለት የህወሓት አመራር አባል የተመራው ልዑክ ደባዜን ከደረሰ በኋላከኦነግ የጠበቀው አቀባበል የስምምነቱ ተቃራኒ ሆነ፡፡
ኦነግ በግልፅ ከህወሓት የተላኩትን ‹‹መርሲነሪዎች›› (ቅጥረኛ ነፍሰ ገዳዮች) ሲል አውግዞ ከወታደራዊ ሰፈሩ በፍጥነት እንዲወጡ አደረገ፡፡ በሁለቱ የአመራር አባላት የተመራው ቡድንም ወደ ትግራይ ተመለሰ፡፡ የቡድኑ መሪዎችም መላው የህወሓት የአመራር አባላትበተገኙበት ሪፖርታቻውን አቀረቡ፡፡ ሁለቱ የአመራር አባላት ክንፈ ገ/መድህን እና ሙሉጌታ ጫልቱ ነበሩ፡፡ ከዚህ ሪፖርት በኋላምህወሓት ከኦነግ ጋር ለመስራት የነበረው ተስፋ መከነ፡፡
የኦሮሞን ድርጅት ፍለጋ


