Friday, March 29, 2013

በየፍርድ ቤቶችሽ የፍትህ ውርጃ ሲፈፀም ዝም አልሽ።

ዶክተር በድሉ ዋቅጅራ
ልዕልና ጋዜጣ
ምንጭ፣ ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም ብሎግ
በቀደም ሳት ብሎኝ፣
ለመጀመሪያ ልጄ ብቻ የፈረንጅ ሸራ ጫማ ገዝቼ ገባሁ። ያለወትሮዬ ማለቴ ለወትሮው ገበያ የምወጣው ሁለቱንም ልጆቼን ይዤ ስለነበረ ነው። ታዲያ ያን እለታ ማታ ትልቅዋ ልጄ ጫማውን ስትለካ፣ የታናሽ እህትዋ አይን ከሚለካው ጫማ ጋር ሲንከራተት ተመለከትኩ፤ ወይም የተመለከትኩ መሰለኝ። ‹‹ከወደድሽው ላንቺም ይገዛልሻል››አልኳት፤ የትንሽዋን ልጄን አይን እየሸሸሁ። በውስጤ አድሏዊነት ተላወሰ። በልጅትዋ ህሊና ውስጥ ይህ ስሜት እንደማያድር ባውቅም፣ የእኔን ሃሳብ ግን ቶሎ ላስወግደው አልቻልኩም። አየሽ ሀገሬ? እንኳን ህዝበ አዳምና ሔዋንን በእኩልነት ቤት ሆኜ አኖራለሁ የሚል ሀገር፣ አንድ ተራ ምስኪን ወላጅ እንኳን በጎጆው አድሏዊነት እንዳይሰፍን ይጥራል። አንቺ ግን ሀገሬ! … አንቺ ግን ዝሆንና ጥንቸል እያፋለምሽ ለአሸናፊው ታጨበጭቢያለሽ፤ ትሸልሚያለሽ።
መቼም ማንም ቢሆን፣ የአደባባይ ውበቱን እንጂ የጓዳ – ጎድጓዳ ገመናውን ሲነግሩት አይወድምና አንቺም ከአደባባይሽ ጀርባ መዝለቄ እንደማይጥምሽ አውቃለሁ። አደባባዮችሽማ ለዜጎችሽ የጋራ ፍትሀዊ መኖሪያነትሽን ይመሰክሩልሻል። መቼም የዜጋ ሁሉ እኩልነት የሚረጋገጠው በህግ ፊት ባለው እኩል መብት አይደል? ይህ ደግሞ ከገጠር ቀበሌሽ አንስቶ እስከ መዲናሽ ባሉ አደባባዮችሽ የሚታይ ነው። የወረዳ ፍርድ ቤት፣ የዞን ፍርድ ቤት፣ የክልል ፍርድ ቤት፣ የፌደራል ፍርድ ቤት፣ ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ ሰበር ሰሚ ችሎት… የፍትህ ቢሮ… ይህ ሁሉ አደባባይሽን ያደመቅሽበት የዜጎችን እኩልነት ማስጠበቂያ ተቋም ነው። ሀገሬ! ለመሆኑ በእነዚህ ተቋማት ምን እያደረግሽ እንዳለሽ ታውቂያለሽ?
አንዳንዴ ሳስበው ፍርድ ቤቶችሽና የፍትህ ተቋማቶችሽ ለዜጎች እኩል ያለመሆናቸውን የምታስታውቂበት ስፍራ ይመስለኛል። ይህን ስትሰሚ እንደምትቆጪ አውቃለሁ። ገመናው ሲሸፈንለት እንጂ ሲገለጥበት የሚወድ ማን አለ! አሁን እስቲ አንቺ ህግ አቁሜያለሁ፣ ዳኛ ሰይሜያለሁ ትያለሽ? ሀገሬ ሙች አፍሽን ሞልተሸ አትይም። ምነው ብትይ እማኝ ጠቅሼ እሞግትበት ሞልቶኛል።
አንድ አትዮጵያዊ ለትምህርት ውጭ ሄዶ ሳለ፣ በፈቀድሽው ከታክስ ነፃ መብቱ ተጠቀመና አውቶሞቢል ገዝቶ መጣ። አንቺንና ያቆምሽውን መንግስት እያሞገሰ አራት አመት በአውቶሞቢሉ ተጠቀመና ተመልሶ ለትምህርት ሄደ።
ባለቤቱ ደግሞ አሁንም አንቺንና መንግስቷን እያመሰገነች ስትነዳ፣ አንድ ቀን በጉምሩክ አሳሽ ጓዶች ተያዘች። መቼም ‹‹ለምን?›› ማለትሽ አይቀርም። የመኪናው ሊብሬ በባለቤትዋ ስም ስለነበር፣ አንቺ በአውቶሞቢሉ መገልገል አትችይም ተብላ፣ ተያዘች። መኪናው ታሰረ። አጣሪ ተቋቋመ። አጣሪው አጣርቶ ‹‹ባለመብቱ ባለቤትዋ በመሆኑ፣ በአውቶሞቢሉ መጠቀም መብትዋ ነው›› ብሎ ሪፖርት አቀረበ። ኮፒው ደግሞ ለሴትየዋ ደረሰ። ታዲያ ሀገሬ ጉዳዩ የቀረበለት የጉምሩክ ባለስልጣን፣ ቀረጡን ትከፍያለሽ አላት። ተያይዞ የቀረበውን ሪፖርት ተመልክቶት እንደሁ ጠየቀችው። አለመመልከቱን፣ ቢመለከተውም እንኳን ሪፖርቱ እግዚአብሔርም ቢመጣ ከመክፈል እንደማያስጥላት፤ ካልከፈለች መኪናዋ ጉምሩክ ውስጥ እንደሚታሸግበት ነገራት።  ሀገሬ፣ ሴትየዋና ባለስልጣኑ ሁለቱም ያንቺ ዜጎች፣ ሁለቱም ኢትዮጵያዊ ናቸው። ቆይ ህግሽ ላይ ‹‹አንድ ኢትዮጵያዊ›› የሚለው ሀረግ ማንን አስበሽ ያሰፈርሽው ነው? እና ሴትዮዋ ሃምሳ አራት ሺህ ብር ከፈለች። ከመክፈልዋ በፊት ግን ሀገሬ ሙች አልቅሳ ለምናዋለች። ከእግዚአብሔር በላይ ያስቀመጥሽውን ዜጋ መለመን እንጂ ምን መፍትሔ አለ! ባለቤትዋ ይህን ሲሰማ መጀመሪያ ያዘነው ባንቺ አይደለም። ባስቀመጥሽው ባለስልጣን ትእቢትና ድንቁርና ተደነቀ። ህግ ፊት አቅርቦ፣ ባለቤቱ በህግ የተሰጣትን መብት የሚጥስበት ከህግ የከበረ መብት እንደሌለው ሊያሳየው፣ ባለስልጣኑን ህግ ፊት ሊገትረው ከአውሮፓ ሲበር መጣ፤ ጠበቃ ቀጠረ።
በቀጠሮው ቀን እሱና ጠበቃው ማልደው ፍርድ ቤት ደረሱ። ተከሳሽ አልቀረበም። የመስሪያ ቤቱ ጠበቃ እንኳን አልቀረበም። ዳኛዋ ሌላ ቀጠሮ ሰጡ። በቀጠሮውም ቀን የቀረበ የለም። ዳኛዋ ባለስልጣኑ ፍርድ ቤቱን ማዋረዱን፣ ከአንዴም ሁለቴ በቀጠሮ አለመቅረቡን ከምንም ሳይቆጥሩ ፍርዱን ገመደሉት። ባለስልጣኑ ትክክል መሆኑን፣ ሴትየዋ መያዛቸው፣ ገንዘቡንም መክፈላቸው አግባብ መሆኑን ፈረዱ።
ሀገሬ፣ ያ ከአውሮፓ የፍትህ ጥማት ሲያበር ያመጣው ሰው፣ በፍትህ መዶሻሽ የተጨፈለቀ ዜግነቱን ይዞ ወደአውሮፓ ተመለሰ። አየሽ ሀገሬ! ለዚህ ነው የምሞግትሽ፤ እኛን ዜጎችሽን ከወባ፣ ከተስቦ ብትፈልጊም ከኤች.አይ.ቪ በላይ የጎዳን በየፍርድ ቤትሽ በህግ የበላይነት ለማያምን  ዳኛ ያስጨበጥሽው መዶሻ ነው።
እንዴ እውነቴን እኮ ነው! ሀገሬ ሙች እውነቴን ነው። ለወባው፣ ለተስቦውና ለኤች.አይ.ቪ.ው እድሜ ለቱጃሮቹ ጓደኞችሽ እንጂ፣ መች መድሀኒት ይገደናል- መርከብ ሞልተው ይልኩልናል። ደግሞ ብንሞትስ! እድር አለን እንቀበራለን። ቆይ እድር ባይኖረንስ! ደግሞ ለመቅበር! አበሻ እንኳን ሞተሽለት ገና በጣር ተይዘሽ፣ ላይ ላዩን መተንፈስ ስትጀምሪ ነው ጉድጓድ መቆፈር የሚጀምረው። ግን ሀገሬ እንዲህ በቁማችን በፍትህ መዶሻሽ ስንሰባበር፣ እነዚህ የወባና የተስቦ መድሀኒት በመርከብ ሞልተው የሚልኩልን ጓደኞችሽ አንቺንም ሆነ መንግስትሽን ሀይ አላሉልንም። እና ሀገሬ፣ ይህ የአንቺ ብቻ ሳይሆን የነሱም ገመና ነው።
ቆይ እኔ የምለው መንግስት ከህግ በላይ ነው እንዴ!? እስቲ ንገሪኝ ሀገሬ- መንግስት የሆኑት ከእኛው መሀከል፣ እንደኛው ዜጋ የነበሩት አይደሉም እንዴ! ዜጎችሽ አይደሉም እንዴ ‹‹መርጣችሁናል›› ብለው መንግስት የሆኑት! ታዲያ ለምንድነው የፍትህ መዶሻሽ እነሱ ላይ ቄጠማ የሚሆነው? ይኽው በአንቺ ውስጥ ከልጅነት እስከ እውቀት ስኖር መንግስት ከሳሽም ተከሳሽም ሆኖ ሲረታ እንጂ ሲፈረድበት አይቼም፣ ሰምቼም አላውቅም። ምን ያስቃል ሀገሬ! በእርግጥ ገንዘብን፣ ወይም ደግሞ ሌሎች ቀለል ያሉ ጉዳዮችን በተመለከተ አንድ ሁለት ፋይሎች በመንግስት ካሳ ከፋይነት እንዲዘጉ አድርገሽ ሊሆን ይችላል። ይህን ተይና እውነት ሀገር ከሆንሽ፣ እስቲ በሰብአዊና በዜግነት መብት ጉዳይ መንግስትን ከስሶ ያሸነፈ አንድ ዜጋ ጥሪ! እረ ጉደኛ ነሽ፣ ሀገሬ!
እኔ የምልሽ የህግ ትምህርት ቤት፣ ምናምን ምን ያደርግልሻል? ለምን አምስትና ስድስት ዓመት ህግ ታስተምሪያለሽ? ለእኛ ለዜጎችሽ ያቆምሽው፣ ህግ እንዳይዛነፍ፣ በየፍርድ ቤቱ ያስቀመጥሽው መዶሻ አናት አናታችንን እያለ ቅስማችንን እየሰበረ፣ ከዜግነት ተራ እንዳያስወጣን አይደለም እንዴ! በአንቺ በሀገሬ ህግ፣ እንኳን መርጠኽኛል፣ ያለ ባለስልጣንና መንግስት ቀርቶ፣ እየሱስ ክርስቶስም ቢሆን፣ ኢትዮጵያዊ ነኝ ብሎ አብሮኝ ቢኖር፣ በህግ ፊት እኩል ነን። አቦ ሀገሬ በፍትህ ስም የምትሰሪው ግፍ በዛ! የምር በዛ። ወይ በቃ የህግ ትምህርት ቤቶችሽን ዝጊና ዳኛ ለምታደርጊያቸው ዜጎች እንዴት የባለስልጣንንና የመንግስትን የስልክ ትእዛዝ ተቀብለው ተግባራዊ ማድረግ እንዳለባቸው አንድ ሁለት ሳምንት አሰልጥነሽ … በቃ!
አንዳንዴ ሳስበው ያ ታከለ የሚመኘውን ምኞት እኮ ሁላችንም ልንመኘው ነው! ሀገሬ መቼም ታከለን ታውቂዋለሽ። ለነገሩ አንዳንዶቹን አውቀሽ ችላ ትያቸዋለሽ እንጂ፣ አንቺ ዜጋሽ መቼ ይጠፋሻል። እሱም አንዱ ፍትህ መከበር አለበት፤ ያለ ህግ የበላይነት ሀገርና ህዝብ አይቆምም፣ ባይ ነው። ታዲያ የውልሽ፣ ከአመት ተመንፈቅ በፊት የቢ.ፒ.አር አሰራሩን ተቃውመሀል ተብሎ ከስራ ታገደ። ሁለት ወር ያለ ስራ ደመወዝ በላ። በሶስተኛው ወር ደመወዙ ቆመ። ሀላፊውን ሊያነጋግር ሄዶ የስራ መልቀቂያ ደብዳቤውን ተቀብሎ መጣ። ታዲያ ያን ሰሞን እቤቴ መጣና፣ ‹‹ገንዘብ አበድረኝ›› ሲለኝ፣ ያው እንደወትሮው ወር መዳረሻ ገዶት ይሆናል፣ ብዬ ‹‹ስንት መቶ?›› ስለው ‹‹ሰባት ሺህ›› አይለኝ መሰለሽ!? መስሪያ ቤቱን ሊከስ እንደሆነም ነገረኝ። ገንዘቡን ለጠበቃና ለአንዳንድ ተጨማሪ ወጪ ፈልጎ ነው። ባንክ በቆጠብኩት ሁለት ሺህ ብር ላይ ከባለቤቴ ቤተሰቦች አምስት ሺህ ብር ተበድሬ ጨምሬ ስሰጠው ‹‹ተው! ይቅርብህ! የመስሪያ ቤቱን ባለስልጣን የሾመው መንግስት ነው። መንግስት ደግሞ ከሶም ተከሶም ይረታል። ሰማይ አይታረስ ንጉስ አይከሰስን አስብ። ቃሉ ቢለወጥም ያው መንግስት ማለት ንጉስ ነው። ቀበሌ፣ ወረዳ፣ ዞን፣ ክልል፣ መስሪያ ቤቶችና መንግስት ያላቸው ልዩነት የተዋረድ ብቻ ነው›› አልኩት። ሀገሬ ሙች አልሰማኝም። እንዲያውም አልሰማ ቢለኝ በየመስሪያ ቤቶቻቸው የተሰየሙ ትንንሽ መንግስታትን ከሰው አቅላቸውን የሳቱ፣ ‹‹ቂጣቸውን በሳንጃ የተወጉ›› ዜጎችን በየዘመኑ ማየቴን፣ ገመናሽን ገልጬ ነገርኩት። አልሰማ ብሎ ፋይሉን በወረዳ ፍርድቤት ከፈተ።
በወረዳ ፍ/ቤትሽ የክስ ፋይል በከፈተ በአራት ወሩ የውሳኔውን ወረቀት አምጥቶ አሳየኝ ሀገሬ ሙች እልሻለሁ ገረመኝ! አንቺ እኮ ትገርሚያለሽ! የፍርድ ቤቱ የፍርድ ውሳኔ ከማህተሙና ከፊርማው ልዩነት በስተቀር፣ ያው የተባረረበት ደብዳቤ ግልባጭ ነው። አዘነ። ሀገሬ ሙች አዘነ። የፍትህ መዶሻሸ ያረፈበትን አናቱን ቀና አድርጎ መመልከት አቃተው።
ታከለ ግን የዋዛ ዜጋ አይደለም። ‹‹እውነትና ንጋት እያደር ይጠራል››ን እየተረተ ይግባኝ አለ። ይኽው ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ሰው ሰርቶ በየወሩ ደመወዝ ሲቀበል፣ እሱ በየደረጃው በሚገኙ ፍርድ ቤቶች፣ የተባረረበትን ደብዳቤ እያፀደቀ ይመጣል።
እና ታከለ ምን ተመኘ መሰለሽ! ሀገሬ ሙች እንደገመናሽ ዝግናኔ የግል ፍርድ ቤት ቢመኝ አይፈረድበትም። አንድ እሁድ ቀን አንድ ካፌ በረንዳ ላይ ተቀምጠን ማኪያቶ ስንጠጣ፣ ከመንገዱ ባሻገር ያለውን የግል ሆስፒታል እየተመለከተ ‹‹በህይወት ዘመኔ ማየት የምመኘው ምን እንደሆነ ታውቃለህ?›› አለኝ። ‹‹ምን›› አልኩት፤ ቁብ አልሰጠሁትም። ‹‹እዚያ ህንፃ አናት ላይ በግል ሆስፒታሉ ስያሜ ምትክ ‹‹ብርሃን ከፍተኛ የግል ፍርድ ቤት፣ መለያችን ይግባኝ አልባ ፍርዳችን ነው!›› የሚል ተጽፎ ማየት። ሀገሬ ሙች አያስቅም! ደግሞ ሰው እንጂ ሀገር ሲስቅም ሲያለቅስም አያምርበትም።
እውነቱን እኮ ነው! በመንግስት ፍርድ ቤት መንግስትን መርታት ካልተቻለ፣ ለምን በግል ፍርድ ቤት አይሞከርም። በቃ ሀገሬ አንቺም የፍትህ ገመናሽን መክላት ካማረሽ፣ በቃ የግል ፍርድ ቤት ክፈቺ። እና የመንግስት ፍ/ቤቶች በዜጎችሽ መካከል ያለን ክስ ይመልከቱ። በማንኛውም ሁኔታ በመንግስትና በዜጋ መካከል ያለን ክስ ደግሞ በግል ፍርድ ቤት እንዲታይ አድርጊ። ያኔ የዜጎችሽ አናት መንግስት ለዳኞችሽ ባስጨበጣቸው መዶሻ አይነደልም። ዜጎችሽ ቀና ብለው ይሄዳሉ፤ ስለፍትህ ስርአትሽም መልካሙን አብዝተው ይናገራሉ። ከሁሉም በላይ ደግሞ አንቺ ደስ ይልሻል። አንቺ ደስ ሲልሽ ደግሞ እኛም መልሶ ደስ ይለናል።
ስለፍትህ ገመናሽ ስናገር የሰሙ አንዳንድ ዜጎችሽ፣ ‹‹እንዴት ሰው፣ ከሰው ገመና አልፎ የሀገርን ገመና አንድ — ሁለት — እያለ ያብጠለጥላል!›› እያሉ ያብጠለጥሉኛል። እኔ ምን ተዳዬ! ሀገሬ አንቺ ራስሽ ገመናሽን መች ሸፈንሽውና እኔ እኮነናለሁ? እንዴ! የምር እኮ ነው የምልሽ! ገመናሽን እንደጋለሞታ ደጃፍ ገልጠሽዋል እኮ! አንቺ ራስሽ አይደለሽ እንዴ ተቃዋሚ፣ አሸባሪ፣ አክራሪ ብለሽ ዜጎችሽን ባሰርሽ ማግስት አኬልዳማ፣ ጀሀዳዊ ሐረካት– ምናምን የሚል ፊልም እየሰራሽ የፍትህ – ገመናሽን ቲቪ ያስገባሽው! እውነት ሀገሬ ያሳፍራል።
ለዚህ እኮ ነው መንግስት የገባበት ክስ የዝሆንና የጥንቸል ፍልሚያ ነው የምልሽ። ያውም ሮጣ የማታመልጥ እግርዋ የተሰበረ ጥንቸል! ሲጀመር ለመንግስት ዝሆንነትን ሰጥተሻል። ጠመንጃ አለው፤ እስር ቤት አለው፤ ቲቪ አለው፤ ራዲዮ አለው፤ ዳኛ አለው፤ አቃቤ ህግ አለው። ይህ ሁሉ ካለኝ ደግሞ እኔም ብሆን፣ ዝሆን መሆን አያቅተኝም። ተቃዋሚ፣ ሽብርተኛ፣ አክራሪ ተብሎ የተመረጠው ደግሞ ጥንቸል ነው። ጥንቸል ከዝሆን ቢፋለም እድሉ አንድ ነው- ሮጦ ማምለጥ። አንቺ ግን ሀገሬ! ጥንቸሎችሽ በፍትህ ስርአትሽ ሮጠው ነፃ የሚወጡበት የመርፌ ቀዳዳ የምታህል ቀዳዳ እንኳን እንዳትኖር፤ ክሳቸው እንኳን ወጉ ተነቦላቸው የእምነት – ክህደት ቃላቸው ሳይሰማ፣ እንዴት እንዳከረሩ፣ እንዴት እንዳሸበሩ ፊልም ሰርተሽ በቲቪ ትለቂዋለሽ። በፍትህ አደባባይ ሮጠው እንዳያመልጡ የጥንቸሎቹን እግር ስብርብር አደርገሽ ማለት ያኔ ነው! .. ኧረ በእውነት ይዘገንናል! አባቶቻቸው ተጠርጥረው ከተከሰሱበት ወንጀል ነፃ የሚወጡበትን ቀን የሚናፍቁ ልጆችን … እናቶቻቸውን.. ጎረቤቶቻቸውን… አስቢ እስቲ! አንቺ በእነሱ ቦታ ብትሆኚና ፍትህን ያስከብርልኛል ያልሽው መንግስት በተጠረጠሩብሽ ላይ፣ እንደዚያ ያለ ፊልም እያቀረበ የፍትህን ጽንስ ለውርጃ ሲዳርግ ብትመለከቺ ምን ትያለሽ! ምንስ ታደርጊያለሽ! ዳሩ አንቺ ሀገር እንጂ ዜጋ አይደለሽም። ዜጋስ ብትሆኚ እግሮችዋ የተሰበሩ ጥንቸል ሆነሽ መታገል ከማይሰለቸው ዝሆን ፊት ብትቆሚ እጣሽ ምንድነው? አቦ ሀገሬ ተይኝ! ገልጠው የማይጨርሱት ገመና አድሎሻል!
(ይቀጥላል)

Ethiopia: EPRDF, no identity and no vision

FOR  IMMEDIATE  RELEASE
March 28 2013

Ginbot 7 Movement for Justice, Freedom and DemocracyFor the past twenty one years, the Tigray People Liberation Front (TPLF) that has no mandate to rule Ethiopia has actually ruled Ethiopia with iron fist dashing on the  Trojan horse,  the  EPRDF ( Ethiopian People Revolutionary Democratic Front).  The EPRDF, a political front; composed of a hodgepodge of ethnically assembled organizations, is a hollow group of ethnic demagogues created by its late leader to materialize his lifelong dream of dividing Ethiopia along ethnic lines. Ironically, the EPRDF that blatantly boasts to have averted the disintegration of Ethiopia, firmly stood up to the dreams of its creator and augmented the fragmentation of Ethiopia, the very country it calls home.
On Saturday March 23, 2013, the EPRDF started its 9th and possibly what could be its last congress with an embarrassing; and to the vast majority of Ethiopians with a pointless theme of – “The Thoughts of Meles”.  In fact, if there is one good cause served by the 9th EPRDF congress, it should be that, the Trojan horse EPRDF proved to the Ethiopian people that it is a party in existence with a borrowed identity that rules over a nation of ninety million people with a dead vision of a deceased man. The EPRDF is a party that lives in the past, failed to cease the moment and has no vision for the future.
The four-day congress that ended on Tuesday came to an end with exactly the same hollowness that it started. To the surprise of its own members and diehard supporters, the four -day congress looked like much of a eulogy of a man (dead for seven months) than an occasion to map a vision for Ethiopia’s future.  Despite all indications of the nation’s chronic problems of ethnic conflict, poverty, human rights abuse, deteriorating living conditions, and alarming outflow of skilled manpower, the EPRDF vowed to extend its grip on power and carry on the same old failed policies of the past. All in all, the handmade toy, the EPRDF, shamelessly told the Ethiopian people that it has no vision of its own and nothing new on its plate.
Ginbot 7, Movement for Justice, Freedom and Democracy not only invalidates the resolution of the 9th congress of the EPRDF, but it also extends its call to the Ethiopian people inside and outside Ethiopia to come together and fight in unison to stop the implementation of a policy that has a hard to reverse the detrimental effect on our nation. Ginbot 7 reiterates its perennial message to the Ethiopian people and to the international community at large that there are much better alternatives to the tested and failed policies of the EPRDF that benefit the interest of the Ethiopian people, the Horn of Africa and all other parties’ involved. The international community, donor nations and most importantly, the EU, United Kingdom and the United States must come to their senses and acknowledge that freedom; justice and democracy are God given human values that the people of Ethiopia thirst for just like the British and the American people.
Ginbot7, Movement for Justice Freedom and Democracy
Public Relation

Thursday, March 28, 2013

ግፍ መሸከም በቃኝ!

March 27.2013
 By:Mekonnen Workineh ,Noway,Oslo
ግራ ጎኔ ቆስሎ ቂም አርግዞ ሲመግል፤
መዳኒት አዋቂ ስር ማሽ ቅጠል በጣሽ ጠፍቶ ደረስኩ የሚል።
አማራ ጠላት ነው ብሎ ሰይሞልኝ ነጻ አውጭው የትግሬ፤
መቀመጫ አጣሁ አሜከላ ሆኖ ሳር ምድሯ አገሬ።
አንገቴን ደፍቼ ኑሮ ልግፋ ባልኩኝ፤
ወለጋ ሲዳሞ ለቀን ስራ ሄጄ ቡና በለቀምኩኝ፤
ጎጆዬን ቀልሼ ኑሮዬን መስርቼ ማስኜ በኖርኩኝ።
ደንብሮ እንደወጣ እንደ ጫካ አውሬ፤
ለምንስ ልደብደብ ለምንስ ልሳደድ ከገዛ ሐገሬ።
የትግሬ ነጻ አውጭ ተከዜን ተሻግሮ ጎንደሬውን ፈጅቶ መሬቱን ሲወረው፤
ወደ ደቡብ ሰፍቶ ወሉን ሲያስብረው፤
አፋር ኦጋዴኑን ኦሮም ደቡቡን፤ አኛክ ዳሰነቹን ደርሶ ሲያሸብረው፡
መታደን ያለበት ወንጀለኛው ን ነው?
አረ አንቀጠቀጠኝ ብርዱ ሆዴ ገባ፤
ህጻን ልጄ ሲወድቅ እያለኝ አባባ፤
ማንሳት እንኳ አቅቶኝ እጄ ሆኖ ሽባ።
እኔ መስሎኝ ነበር ትግሬ ወገኔ ነው፤
አኔ ብዬ ነበር ትግሬ ወንድሜ ነው፤
ነጻ አውጭው ሲፈጀኝ ተው አላለ ምው?
ሰው በማንነቱ ሰው በዘሩ ሲፈጅ ሰምቼ ነበረ ታሪኩን እንደቀልድ፤
አሁን ባይኔ አየሁት የትግሬ ነጻ አውጭ ነፍሰ ጡር ጥሎ ሲያርድ።
ቁልጭ ብሎ ሚታይ ፍንተው ያለው እውነት፤
የትግሬ ነጻ አውጭ ፍጹም አይፈልግም አማራን ለማየት፤
ቀን ከሌት ይሰራል ኢትዮጵያን ለማጥፋት፡
እኔ ወይ ወያኔ ማ መጥፋት አለበት?
ሐገሬ ተራራው ስርጡ ተረተሩ፤
ክትክታ አጋሙ አሸዋ ኮረቱ
ሁሉም መሣሪያ ነው ስትቆርጥ ልቢቱ።
እኔም ሰው ነኝ እኮ ይከፋኝ ያመኛል፤
በደል እስከመቼ ይታዘልልኛል።
በገዛ ሐገሬ አትኖርም ስባል፤
እንደ ልፋጭ ስጋ ተቆርጬ ስጣል።
ትከሻ የለኝም ይህን የሚሸከም፤
ተናንቄ ልሙት ትንፋሼም ትጨልም።
የትግሬ ነጻ አውጭ ጥንስሱ እየፈላ፤
አላስቀምጥ አለኝ ግማቱ እያስጠላ።
በቃኝ በቃኝ በቃኝ ሸክም በዝቶብኛል፤
ይህ አንገቴን መድፋት ለዚህ አብቅቶኛል፡
ልጄንም ሚስቴንም ማዳን አቅቶኛል፤
የትግሬ ነጻ አውጭ በጠራራ ፀሃይ እኔኑ ደፍሮኛል፡
አገር አገር ብዬ ጥቃቴን ባፍው፤
የትግሬ ነጻ አውጭ ፈነጨብኝ ምነው?
አባባ ዳቦ ሲል የምሰጠው የለኝ፤
ወንድም ጋሼ ስትል እቴን መች አስጣልኩኝ።
ልጄም እንዳሻህ ሁን አህቴም እንደዛው፤
የትግሬ ነጻ አውጭን ሄጄ ልፋለመው።
ጃሎ በል ወገኔ ወርደህ በለው በለኝ፤
የባንዳ ጥራጊ ከትቢያ ሲቆጥረኝ።
አንደበትም የለኝ አልናገር ዳግም፤
ሰው እስክሆን ድረስ አደባባይ አልቆም፤
የባንዳን ጥራጊ በፍልሚያ ገጥሜ፤
ሰው ሆኜ መጣለሁ ሲያገግም ህመሜ።
ከመኖሪያ ቄያቸው በመሳደድ፤ በመታደን፤ በመገደል ላይ ላሉ አማርኛ ተናጋሪ እትዮጵያውያን እና ሲጓጓዙ መኪና ተገልብጦ ላለቁ እና አሰከሬናቸውን አውሬና አሞራ ለተቀራመተው ወገኖቼ መታሰቢያ ትሁንልኝ

Monday, March 25, 2013

The Dragon Eating the Eagle’s Lunch in Africa?

by Alemayehu G. Mariam

Flight of the Eagle and pursuit of the Dragon
 China's unprincipled opportunism in Africa.authoritarian stateIn June 2011, during her visit to Zambia U.S. Secretary of State Hilary Clinton pulled the alarm bell on a creeping “new colonialism” in Africa. While dismissing “China’s Model” of authoritarian state capitalism as a governance model for Africa, she took a swipe at China for its unprincipled opportunism in Africa. “In the long-run, medium-run, even short-run, no I don’t [think China is a good model of governance in Africa]…We saw that during colonial times, it is easy to come in, take out natural resources, pay off leaders and leave, …And when you leave, you don’t leave much behind for the people who are there. We don’t want to see a new colonialism in Africa…”
It seems the Eagle has finally taken a good look at the sidewinding Dragon eating its lunch in Africa. The U.S. is in stiff competition not only in Africa but also in the “world’s least explored” country. Clinton minced no words in telling the U.S. Senate Foreign Relations Committee, “We are in a competition for influence with China; let’s put aside the moral, humanitarian, do-good side of what we believe in, and let’s just talk straight realpolitik… Take Papua New Guinea: huge energy find … ExxonMobil is producing it. China is in there every day in every way, trying to figure out how it’s going to come in behind us, come under us.”
For the past decade, the U.S. has been nonchalant and complacent about China’s “invasion” and lightning-fast penetration of Africa. It was a complacency born of a combination of underestimation, miscalculation, hubris and dismissive thinking that often comes with being a superpower. But the U.S. is finally reading the memo.
Meanwhile, China is zooming along the African highway of “opportunism” with steely resolve and an iron fist sheathed in velvet gloves lined with loans, aid and expensive gifts.  In July 2012, Chinese President Hu Jintao at the Opening Ceremony of the Fifth Ministerial Conference of the Forum on China-Africa Cooperation proudly proclaimed his country’s economic prowess in Africa. “China’s trade with and investment in Africa have been expanding. In 2011, our two-way trade reached 166.3 billion U.S. dollars, three times the figure in 2006. Cumulative Chinese direct investment in Africa has exceeded 15 billion U.S. dollars, with investment projects covering 50 countries.” He added, “China and Africa have set up 29 Confucius Institutes or Classrooms in 22 African countries. Twenty pairs of leading Chinese and African universities have entered into cooperation under the 20+20 Cooperation Plan for Chinese and African Institutions of Higher Education.”
In 1980, China’s total economic investment in Africa hovered around $USD1 billion; and 20 years later rose only to $USD10 billion. In 2010, China and Ghana signed infrastructure-related loans, credits and made other arrangements valued at about $15 billion. In 2009, China signed a $6 billion loan agreement with the Democratic Republic of the Congo for infrastructure projects. In 2010, Chinese banks extended nearly $9 billion in loans and other types of financing to Angola for various projects. The Angolan government in turn used its oil credit line to commission the State-owned China International Trust and Investment Corporation to build a ghost town outside of the capital at a cost of $USD3.5 billion.  (To see the video of the Angolan ghost town click here.)  In 2011, Chinese firms accounted for 40% of the corporate contracts in Africa compared to only 2 percent for U.S. firms.  According to a report issued by the South African Institute of International Affairs, between 2003-2009, there were between 583,050–820,050 Chinese living, working and doing business in 43 African countries. Today China is Africa’s largest trading partner as the U.S. recedes fast in the rear view mirror.