Monday, August 5, 2013

ለንጹሃን የደም ጥሪ ተገቢው ምላሽ ትጥቅ አንስቶ ነፍሰ ገዳዮችን መፋለም ብቻ ነው!

August 5, 2013

የግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል (መግለጫ)
Ginbot 7 Popular Force
Ginbot 7 Popular Force logoከሃምሌ 26 _ 2005 አንስቶ  ይህ መግለጫ እስከወጣበት እስከ ሃምሌ 28_ 2005 አ.ም እለት የወያኔ ዘረኛ ጉጅሌ ቅጥር ነፍሰ ገዳዮቹን በማሰማራት በመላው ኢትዮጵያ፣ በእስልምና እምነት ተከታይ የሃገሪቱ ዜጎች  ላይ በስፋት የግድያ እርምጃ እየወሰደ ነው። ክቡር ህይወታቸውን በግፈኛው የወያኔ የአፈና ሃይል ያጡት ወገኖች ቁጥር በርካታ ሆኗል። ክፉኛ የቆሰሉት ወገኖቻችን ቁጥር ከተገደሉት እጅጉን የገዘፈ ነው። ፍጹም አረመኔያዊነት  በተሞላው መንገድ በወያኔ ቅልብ ጦር የተቀጠቀጡትና እንደከብት ተሰብሰብው በየእስር ቤቱ የታጎሩት ወገኖቻችን ቁጥር በሽዎች የሚቆጠር ሆኗል። እጅግ ሰላማዊና  ስልጡን በሆነ  መንገድ ፍትሃዊ ጥያቄ ባነሱ ወገኖቻችን ላይ የደረሰውን እልቂት የግንቦት 7  ህዝባዊ ሃይል የራሱ እልቂት አድርጎ  ያየዋል። የደረሰባቸውን  መከራና እንግልት የራሱ መከራና እንግልት አድርጎ  ወስዶታል።
የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል ወያኔን አያወግዝም ወይም ወያኔ በኢትዮጵያውያን ላይ የሚፈጽመውን ግፍ በገንዘብና በስልጠና  በዲፕሎማሲ ድጋፍ የሚያበረታቱን የምእራብና  ሌሎች የወጭ መንግስታት ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ አይማጸንም። ባለፉት 22 አመታት ውግዘትና መማጸን የትም እንዳላደረሱን በሚገባ እናውቃለንና። ግንቦት 7  ህዝባዊ ሃይል ደግሞ ደጋግሞ  ግልጽ እንዳደረገው የኢትዮጵያ  ህዝብ መከራ የሚያበቃው ህዝብ የወያኔን በእብሪት የተሞላ ግፈኛ ማንነት የሚመጥንና  የሚስማማ የትግል ስልት መርጦ አምሮ  ወያኔን ታግሎ  በመደምሰስ ብቻ ነው። ሙስሊሙም ሆነ የሌሎች እምነት  ተከታዮች መረዳት የሚገባን ወያኔ ስላማዊና  ስልጡን ከሆነው የእኛ አለምና  መርህ ጋር የማይተዋወቅ ዘረኛ  ገዳይ  ሃይል መሆኑን ነው። ይህ በእብሪትና  በድንቁርና የታጀለ የወያኔ  ሃይል የእናንተን ትእግስት ከፍርሃት፣ አርቆ አሳቢነታችሁን ከሞኝነት ጋር አስተሳስሮ የሚያይ ነው። “የምንገድልለት አላማ ባይኖረን የምንሞትለት አላማ አለን” የሚለውን ድንቅና ክቡር እመነታችሁን ወያኔ የሚያየው እናንተን በመግደል ፍትሃዊ ጥያቂያችሁን ማዳፈን ይቻላል በሚል ትርጓሜ ነው።ወያኔ ይህን የተቀደሰ እምነታችሁንና እንዲሁም  ቅንነትና ትእግስታችሁን ለእናንተ የሚመጥን ስልጡን ምላሽ  ማፈላለጊያ አድርጎ  አያየውም። አላየውም።
የትግል ስልት የሚቀየሰው የባላንጣን ማንነት በሚገባ ግምት ውስጥ በማስገባት እንጂ እኛ የምንፈልገው የትግል ስልት ስለሆነ  ብቻ መሆን አይችልም ብለን እናምናለን። እኛ በግንቦት 7 ውስጥ የተሰባሰብን አባላት የወያኔን የእብሪት አመጽ ማስቆም የሚቻለው የወያኔ አፈሙዝ ብቻ   ሳይሆን የእኛም ጠመንጃ እሳት የሚተፋ እንደሆነ በተግባር በማረጋገጥ ብቻ ነው የሚል ጽኑ እምነት አለን። ምንም አይነት የስልጣኔና የሞራል ማእቀብ  ከማይገዛው  ወያኔን ከመሰለ እኩይ ሃይል እራስን ከጥቃት መከላከል ብሎም በወያኔ መቃብር ላይ ሰላምና ነጻነት ማስፈን የተፈጥሮና የዜግነት መብታችን ብቻ ሳይሆን የአላህም ፈቃድና  ፍላጎት ለመሆኑ ጥርጥር የለንም።  በዚህ አጋጣሚ የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል ለእስልምና ተከታይ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ሆነ ለመላው የኢትዮጵያ  ህዝብ የሚያስተላልፈው ጥሪ የሚከተለው ነው። “የወያኔን የእብሪት አመጽ በፍትሃዊና ህዝባዊ አመጽ ለመመከት በያላችሁበት ተደራጁ። የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይልን ተቀላቀሉ። የወያኔን የግፈኛነት እብጠት በህዝባዊና ፍትሃዊ የመሳሪያ አመጽ እናስተንፍስ” የሚል ነው።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!!
ሞት የንጹሃን ደም በከንቱ ለሚያፈሱ በሙሉ !!!!

Tuesday, July 30, 2013

Record set straight on Ethiopia’s Oromo people

July 30, 2013
Ethiopia is one of the most historic nations on the face of this earthEthiopia is one of the most historic nations on the face of this earth, but writers are creating a stream of confusion about the breakdown of Ethiopians, particularly the Oromo people, and many are losing site of the truth, experts say.
Professor Feqadu Lamessa, a former Adama University professor and writer, says Qatar-based al Jazeera has published several articles concerning the Oromo people of Ethiopia. Praising the coverage, Lamessa believes it forces Ethiopian authorities to address human rights abuse in the country and to let them know that the world is watching.
“Oromos and other Ethiopians have been struggling for equal rights and democracy for decades. While it is important to report about Oromo people’s background and historical perspectives, it is however vital that we report accurate information. Instead of benefiting us, reporting inaccurate or biased information can actually harm our struggle for democracy. Instead of creating national consensus and peace, it can instigate bitterness and anger.”
Lamessa says there are some general inaccuracies that are reported frequently. For example, it is generally believed that between 1868 and 1900, half of all Oromo were killed, approximately five million people. The professor says this is not true, and that in fact it was a case of ill-equipped soldiers from the south fighting better-equipped forces from the north with a larger European influence. Lamessa says it was not genocide.
He also says Oromo people have never been a predominantly Muslim, yet it is frequently reported today that they in fact are, “The latest official 2007 census showed that around 48% of Oromos practice Christianity (Both Orthodox & Protestant) while around 47% of Oromos practice Islam.”
Lamessa says it is widely believed that Abyssinians labeled Oromos with the derogatory word ‘Galla,’ and that for many decades, the falsity has been used by Oromo separatists to build emotional resentment among Oromos against Semitic Abyssinians, which include Amharas, Tigrayans and Gurages. “The fact is the derogatory word ‘Galla’ was first used by Arab and Muslim Somalis to describe Oromos as ‘gal’ meaning ‘outsiders’ and ‘Pagans.’”
Lamessa says the label was used by Muslims during Oromo migration because Oromo people had their own religion which the Muslims believed was paganism. Over time, the derogatory word was gradually adopted and used by other Ethiopians.”
There are other points that Lamessa has addressed, including the popular claim made by secessionist Oromo politicians that Oromo people were colonized by another ethnic group.

Monday, July 29, 2013

History 101: Fiction and Facts on Oromos of Ethiopia

July 29, 2013
Prof. Feqadu Lamessa for Salem-News.com
(A guide for foreign journalists on Oromos and Ethiopian history)
(ADAMA, Ethiopia) – Recently, the Qatar-based media al Jazeera has published several articles concerning the Oromo people of Ethiopia. It is the first international media outlet to extensively report on our people and it should be praised for bringing our cause to the world stage.
Ethiopia officially known as the Federal Democratic Republic of EthiopiaOne of the benefits of this exposure is it forces Ethiopian authorities to address human rights abuses in the country and to let them know that the world is watching. Oromos and other Ethiopians have been struggling for equal rights and democracy for decades. While it is important to report about Oromo people’ background and historical perspectives, it is however vital that we report accurate information. Instead of benefiting us, reporting inaccurate or biased information can actually harm our struggle for democracy. Instead of creating national consensus and peace, it can instigate bitterness and anger.
One of the reasons al Jazeera reported inaccurate information about Oromo history is because it depended on one-sided sources, especially from members or supporters of Oromo groups outside of Ethiopia (diaspora OLF, OFDM etc). But nobody can blame al Jazeera media because most people inside Ethiopia would be too scared to speak or contribute. The only option al Jazeera or any foreign media has is to use diaspora/refugee/external sources outside Ethiopia. This is a dilemma all foreign media outlets face while reporting about third-world countries like Ethiopia.
For educational purposes, some corrections are provided below to fix inaccuracies reported on al Jazeera media regarding Oromo history and our struggle for democracy. The corrections below are supported by non-political scholars, but they might be rejected by biased politicians (both from ruling party and from opposition party) for the obvious reasons. However, they are based on historical textbooks, European authors and scholarly accounts.
Fiction #1:
“Between 1868 and 1900, half of all Oromo were killed, around 5 million people”
Fact #1:
This is one of the most repeated inaccuracies, usually told by Secessionist Oromos, radical ethno-nationalist politicians outside the country or pro-OLF history revisionist websites like gadaa.com et al. However, the undisputed fact is that even the total Ethiopian population (the sum of dozens of ethnic groups) was much less than 5 million in the late 1800s, let alone one ethnic group being 10 million. So claiming that 5 million ethnic Oromos were killed by Emperor Menelik’s forces does not add up. The truth is several thousand Oromos were in fact killed during battles of that era. It was not a “genocide” as some politicians claim but it was a massacre of the ill equipped southern forces defeated by the Shewan military of Emperor Menelik which had more European weapons. Throughout those decades, the truth is more Oromos were killed by other Oromos than by non-Oromos because competing Oromo Clans often traded for weapons to have an upper hand against their local competitors, who were often their fellow Oromo and Sidama neighbors. And it was not the first lop sided victory of that era in Africa because various communities from all corners of Ethiopia had attacked one another during the “resource battles” and whichever group had more modern weapons had the upper hand. To summarize, Professor Mengistu Paulos of Jimma University said it best when describing right-wing Oromo liberation philosophy:

Power Africa? Empower Africans!

July 28, 2013
Power, power, power…
When President Obama recently visited Africa, he announced a “Power Africa” initiative.  In his Cape Town University speech, he proclaimed,  “I am proud to announce a new initiative. We’ve been dealing with agriculture.  We’ve been dealing with health. Now we’re going to talk about power: Power Africa, a new initiative that will double access to power in sub-Saharan Africa. Double it.  We’re going to start by investing $7 billion in U.S. government resources. We’re going to partner with the private sector, who themselves have committed more than $9 billion in investment.”
In the speech, President Obama used the word “power” 21 times in a variety of contexts. He philosophized about “power that comes from acting on our ideals” and the  “power of human beings to affect change”. He urged Africans to act “through the power of your example”. He encouraged support for programs “that empower women”. He mildly chided “those in power who make arguments to distract people from their own abuses.”
He puzzled over “what it will take to empower individual Africans” and enable Africans to have the “power to feed themselves.” He pleaded for “unleashing the power of entrepreneurship and market” and the creation of “partnership that empowers Africans.” He spoke about “the power to prevent illness and care for the sick” and “the power to connect their people to the promise of the 21st century.”
He lamented “Africa’s lack of access to power” and the need “to have power.”  He “talked about power — Power Africa” and “doubling access to power in sub-Saharan Africa.” He pitied those Africans who “live currently off the power grid.”
He wistfully spoke about Nelson Mandela “leaving power” which “was as profound as his ability to claim power”. He spoke of Mugabe’s “corruption of power” and Zimbabwe’s economic collapse.
To power Africa or to empower Africans, that is the question
Africa has a power problem. There is no question about that. Africa needs protection from thugs-cum-leaders who abuse power, misuse power, confuse power and excuse and justify their abuse and misuse of power. President Obama is already powering Africa. Every year, he hands out billions of dollars to Africa’s worst dictators (excuse me, he calls them “partners”) who abuse power in countries like Ethiopia.  Africa needs people power not thugs in power.
On second thought, Africa does not have a power problem.  Africa has a problem of powerlessness. The people are powerless against thugtators who use power to abuse their human rights. Africans are powerless against the powerful forces of corruption – officials and their cronies who “illicitly transfer” (steal and stash) tens of billions of dollars in foreign banks. For instance, “Ethiopia lost $11.7 billion to outflows of ill-gotten gains between 2000 and 2009” and  “in 2009, illicit money leaving the country totaled $3.26 billion.” Africans are powerless and disempowered against powerful election thieves who claim electoral victory by 99.6 percent. Africans are powerless against powerful warlords who seek to divide them along ethnic, religious, linguistic and regional lines. Yes, Africa’s powerless have a big problem with Africa’s powerful thugtators.
President Obama does not seem to get it. The question is not whether to power Africa but how to protect powerless Africans from those dictators America has powered and empowered by doling out billions of dollars in aid, loans and technical assistance every year. If he wants to power Africa, he should begin by empowering ordinary Africans against those who abuse and misuse their power. He should power up the youth grid that remains unused, abused and disused by those who manage the political power grid. He should use the billions of dollars of annual aid to disempower the few powerful African thugtators and empower the hundreds of millions of African youth.
Last week, in his New York Times opinion piece, Eskinder Nega, the symbol of press freedom in Ethiopia and Africa, made a simple but effective recommendation to President Obama: “I propose that the United States impose economic sanctions on Ethiopia (while continuing to extend humanitarian aid without precondition) and impose travel bans on Ethiopian officials implicated in human rights violations.” This proposal is in line with established U.S. policy. Beginning in 2001, the U.S. has imposed “targeted sanctions on the Government of Zimbabwe, including restrictions on U.S. support for multilateral financing, financial sanctions against selected individuals and entities, travel sanctions against selected individuals, a ban on transfers of defense items and services, and a suspension of non-humanitarian government-to-government assistance.” The official reason for these sanctions is the “Zimbawean Government’s increasing assault on human rights and the rule of law.” The human rights record of the regime in Ethiopia is far worse than the regime in Zimbabwe. That is a fact that can be demonstrated. President Obama should understand that what’s good for the goose is good for the gander.

Sunday, July 28, 2013

Tracing Woyane’s Anti-Ethiopianism to the Italo-Ethiopian War

July 28, 2013
by Selam Beyene, PhD
The history of Ethiopia is replete with contradictions and paradoxes. There are accounts galore of heroism and meekness, patriotism and treachery, devotion and apathy, and, above all, fear of God and acts of
brutality in that ancient country. These chronicles may help provide clues about the root causes of the Woyane anti-Ethiopia schema and the appropriate plan of action needed to deracinate them.

By anti-Ethiopianism we purport the systematic and government-sanctioned weakening of the national fabric by pitting one ethnic group against another, as was witnessed recently in such areas as Benishangul-Gumuz and Gura Ferda zones. Anti-Ethiopianism is the appalling government policy of dislocating natives from their ancestral lands and transferring national wealth to foreigners at dirt cheap prices. It is anti-Ethiopianism to frame a constitution whose central object is to promote the disintegration and land-lockedness of the country.  Most importantly, anti-Ethiopianism implies the deviant system of government under which all major economic, political and military institutions are controlled by the minority Woyane group, and through which fundamental human rights are suppressed and the people are denied their basic rights to participate in free and fair elections.
Confucius sagaciously advised: “Study the past if you would define the future.” Accordingly, when we consider the current predicaments of the country, which are characterized by ethnocentrism, totalitarianism, corruption, nepotism and absence of a feeling of Ethiopian patriotism amongst the rulers; and, most importantly, when we search for a viable solution to them, we should go no further for clues and explanations than the recent past events, beginning with the invasion of Italy in 1935-1940.
Much has been documented about the infamous Fascist aggression by notable Ethiopian and Western historians, journalists and novelists, as well as other writers who had taken active parts in the actual war. While well-researched history books and journal articles may serve as the ultimate sources for academic exercise, there is considerable information that may be gleaned from anecdotal accounts narrated by individuals based on their personal experiences. In this regard, we are fortunate to have at our disposal now the writings of three foreigners who had the opportunity to witness firsthand the savagery of the Fascist aggression, the heroism of the Ethiopian fighters, and the betrayal by local collaborators.
The three foreigners, whose paths had crossed several times in the battles of Tembien, Maichew and other fronts, had fought on the side of Ethiopia under the leaderships of such eminent Ethiopians as Ras Kassa Hailu Darge, Ras Seyoum Mengesha and Ras Mulugeta Yiggezu, the War Minister. In so doing, they were able to record considerable historical data and to leave behind intriguing accounts of bravery and treachery that could inform present and future researchers seeking answers to some of the most complex questions about present-day Ethiopia. Most importantly, they provide critical insights into the underlying reasons for the anti-Ethiopian agenda Zenawi and his Woyane entourage successfully exploited to catapult themselves to power; the continued damage to the long-term viability of the country that is caused by the misguided fiscal, economic, educational and military policies implemented by the TPLF-led regime; and the institutionalization of ethnic-based governance that is portentously promoted to nurture inter-ethnic animosity among brothers and sisters who have lived in relative harmony for many centuries.

Saturday, July 27, 2013

ሰበር ዜና


=======
የአንድነት ፓርቲ አመራሮች ቤት በፖሊሶች እየተበረበረ ነው
=======================================
- ብርበራው ቀኑን ሙሉ እንደሚደረግ ታውቋል
===============================
በደቡብ ወሎ ዞን በሀይቅ ከተማ የሚገኙ የአንድነት ፓርቲ አመራሮችና አባላት ቤት ላይ ዛሬ ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ ብርበራ እንደተጀመረ የዞኑ የአንድነት ፓርቲ አመራሮች ለፍኖተ ነፃነት አስታወቁ፡፡
የአንድነት ፓርቲ የወረባቡ ወረዳ ሰብሳቢ አቶ እድሪስ ሰኢድ ለፍኖተ ነፃነት እንዳስታወቁት ዛሬ ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ “የጦር መሳሪያ ሰውራችኋል” በሚል ፖሊሶችና ሚኒሻዎች በሀይቅ ከተማ ባሉ ከ16 በላይ በሚሆኑ የአንድነት ፓርቲ አመራሮችና አባላት መኖሪያ ቤት ውስጥ ብርበራ አካሂደዋል፡፡ ብርበራው ከተካሄደባቸው አመራሮች መሀከል አንዱ የሆኑት የወረዳው የአንድነት ፓርቲ የፋይናንስ ኃላፊ አቶ አራጌ ሑሴን ለሪፖርተራችን እንደገለፁት 5 ፖሊሶችና 1 ሚሊሻ ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምረው መኖሪያ ቤታቸውን ፈትሸዋል፡፡ አቶ አራጌ ሁሴን አክለውም “እኔ ሰላማዊ ሰው ነኝ ምንም አታገኙም አልኳቸው፤እንዳልኩትም 2 ሰዓት የፈጀ ብርበራ አድርገውም አንዳች ሳያገኙ ወጥተዋል” በማለት ገልፀዋል፡፡
“ብርበራው መንግስት በአንድነት አባላት ቤት ውስጥ የጦር መሳሪያ አገኘሁ በሚል የተለመደ ድራማ ለመስራት እንደተዘጋጀ የሚያስረዳ ነው” ያሉት የአንድነት ፓርቲ የደቡብ ወሎ ዞን ሰብሳቢ አቶ ብስራት አቢ ኢህአዴግ የደቡብ ወሎ ህዝብ በግዳጅ አንድነት ፓርቲን እንዲያወግዝ በተለያዩ ከተሞች ስብሰባና ሰላማዊ ሰልፎችን እንደጠራ አስረድተዋል፡፡ በአንድነት አባላት ቤት የሚደረገው ብርበራ እስከ ምሽት ሊቀጥል እንደሚችልም ለፍኖተ ነፃነት የደረሱ መረጃዎች አመላክተዋል፡፡

Thursday, July 25, 2013

የሰማያዊ ፓርቲ ጥያቄ እና የመንግስት ምላሽ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ገፅ 3 (አጀንዳ)


የሰማያዊው ፓርቲ ጥቁር ተግባራት
ሰማያዊ ፓርቲ በጠራው ሕዝባዊ ሰልፍ ላይ ያቀረባቸው ጥያቄዎች የተሰላፊዎች ጥንቅርና መሰረታዊ ዓላማ በእጅጉ አነጋጋሪ ለሆኑ ጉዳዮች መነሻና መንደርደሪያ ሆነውኛል።
ሰማያዊ ፓርቲ ከአንድነት ፓርቲ ባለመስማማትና በልዩነት ራሳቸውን ያገለሉ፣ መርህ ይከበር በሚል ተሰባስበው የነበሩ ግለሰቦች የመሰረቱት ፓርቲ ነው፡፡ ወደ ኋላ ስንመለስም በ1997 ዓ.ም ቅንጅትን ከመሰረቱትና የከሸፈውን አመጽ በማስተባበርና በመምራት ከፊትና ከኋላ የነበሩ፤ ዛሬ ደግሞ የቀድሞውን ማንነታቸውን ሳይለቁ በአዲስ መልክና በአዲስ ኮፍያ ለመንቀሳቀስ እየሞከሩ ያሉ ናቸው፡፡
አንድ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲ ሕገ መንግስቱ በሰጠው መብት በሰላምና በሕጋዊ መንገድ ሕጉንና ስርዓቱን አሟልቶ መንቀሳቀስ ይጠበቅበታል፡፡ ሰማያዊም ፓርቲ ሆነ ሌሎቹ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በውጭ ከሚገኘው ጽንፈኛና አክራሪ ኃይል ጋር በመቀናጀት በአረቡ ዓለም የታየውን አብዮት ወደ ኢትዮጵያ እናመጣለን በሚል ለረዥም ጊዜያት ውስጥ ውስጡን ሲንቀሳቀሱ ቆይተዋል፡፡ ሆኖም እውነቱን የተረዳው ሕዝብ በአንድም ሆነ በሌላ መልኩ ይህንን ሊቀበላቸው አልፈቀደም፡፡
ከውጭ የአሸባሪው ግንቦት ሰባት ቴሌቪዥን ጣቢያ «ኢሳት» ባለፉት አመታትም ሆነ አሁን ሰማያዊ ፓርቲ የጠራውን ሕዝባዊ ሰልፍ አይነት እንዲካሄድ በዚህም ጠንካራ ጸረ-መንግስት እንቅስቃሴና አመጽ በአዲስ አበባና በክልሎች እንዲቀጣጠል፤ሁኔታዎች ከቁጥጥር ውጭ እንዲሆኑ፤ ሀገሪቷ ሰላሟ ደፍርሶ ወደ ሁከት፣ ብጥብጥና ስርዓተ አልበኛ ሁኔታ እንድታመራ፤ ያልፈነቀሉት ድንጋይ ያልጫሩትና ለማቀጣጠል ያለኮሱት እሳት የለም፡፡ አሁንም ሕዝቡ የተረጋጋ ሰላማዊ ሕይወቱን፣ የሀገሩን ሰላምና ደህንነት አጥብቆ የሚፈልግ በመሆኑ ይኸው እኩይ ሙከራቸው ሳይሳካ ቀርቷል፡፡
ካለፈው አመት ጀምሮ በአዲስ አበባ የሚገኙ ተቃዋሚዎች በርቀት ካለው ጽንፈኛው አክራሪ ሀይል ጋር በውስጣዊ ትስስር በመቀናጀት፤ አጀንዳ በመጋራት ሌላው የሴራ መንገድ አላዋጣቸው ሲል፤የሙስሊም ወንድሞቻችንን ትግል እንደግፋለን፤ ከጎናቸው እንሰለፋለን፤ መንግስት በሙስሊሞች ጉዳይ ጣልቃ ገብቷል፣ የታሰሩት ይፈቱ፣ ወዘተ የሚሉ መፈክሮችን በአገር ውስጥ ደጋፊዎቻቸው በጋዜጦች በዌብ ሳይቶች (በተለይም በአረቡ ዓለም መገናኛ ብዙሀንና ድረ ገጾች) በመጠቀም የፖለቲካ ድጋፋቸውን ለማስፋት በእጅጉ ደክመዋል፡፡አሁንም ገፍተውበታል፡፡
በአሜሪካና በሌሎች አገሮች የሚገኙ የጽንፈኛው ግንቦት ሰባት አክራሪ ቡድን አባላትና ደጋፊዎች በጅምላው የሙስሊሙን ጥያቄ እንደግፋለን በሚል ስብሰባ አካሂደዋል፣ ሰልፍ ጠርተዋል፡፡ ከሂጅራ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር የገንዘብ እርዳታ አሰባስበዋል፡፡ ይህንን ሁሉ ሸብ ረብ ሲያካሂዱ በኢትዮጵያ የአክራሪ እስልምና አደጋ መሰረት እየጣለና የሸረሪት ድሩን እያደራ መሆኑን እያወቁም ቢሆን ይክዳሉ፡፡
እነሱ የሚፈልጉት ምንም ሆነ ምን ከጎናቸው ተሰልፎ ኢሕአዴግን የሚጥል ሀይል ማበራከት በሚለው የጨለማ አስተሳሰብ የተቃኘ ነው፡፡ ስለዚህም ጥቂት አክራሪ ሙስሊሞች በየሳምንቱ የዓርብ ጁምአ ጸሎት፤ለስግደት በወጣው ሕዝበ ሙስሊም መካከል መፈክር በማሰማትና በማስተጋባት ሲያካሂዱት የነበረውን እንቅስቃሴ ተቃዋሚው ሀይል አይኑን ጨፍኖ ሕጋዊ ጥያቄ ነው በማለት ድጋፉን እየሰጠ ይገኛል፡፡ ይህንኑ አንድነት፣ መድረክና ሰማያዊ ፓርቲ በአይዞአችሁ ባይነት እያጋፈሩና ስፖንሰር እያደረጉት ይገኛሉ፡፡ ጉዳዩ ኢሕአዴግን የመደገፍ ወይንም ያለመደገፍ ጉዳይ ሳይሆን የአክራሪ ሙስሊሞች እንቅስቃሴ በኢትዮጵያ መከሰት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ሕልውናና የደህንነት ጉዳይ መሆኑን ከጥላቻ ወጥቶ ማስተዋል ያልቻለ ተቃዋሚ ይሏል ይህ ነው።
መንግስትና የኢትዮጵያ ሕዝብ የችግሩን መሰረታዊነትና አሳሳቢነት በውል የተረዳው በመሆኑ ይህንን አደጋ ለመቅረፍ በጋራ እየሰሩ ይገኛሉ፣ ውጤታማም ሆነዋል፡፡ ምንም እንኳ ሰማያዊ ፓርቲ ያካሄደው ሕዝባዊ ሰልፍ ለሌሎች ጸረ ሰላም ኃይሎች አጀንዳ ማራመጃነትና መጠቀሚያነት ያገለገለ ቢሆንም። ሁከትና ብጥብጥ ሳይነሳ፤ በትዕግስት ማስጨረሱ የመንግስትን ብስለት በገሀድ ያረጋግጣል፡፡
ይህንን እንደ መልካም አጋጣሚ የወሰደው ጽንፈኛ ተቃዋሚ በድርጊቱ በመግፋት በክልሎችም ሰልፉን እያስተባበረ ይገኛል፡፡ መድረክ በመቀሌ ሰልፍ ለማድረግ ተከለከልኩ ሲል አንድነት ደግሞ ሁለት ወር የሚዘልቅ ሰልፍ በየክልሉ ለማድረግ ፕሮግራም አውጥቷል፡፡ የግብፆች እቅድ፤በአገር ውስጥ ተቃዋሚ በመጠቀምና በገንዘብ በመርዳት መንግስትን ማዳከም፤መወጠር የሚለው ስትራቴጂያቸው በገሀድ ነፍስ ሲዘራ እያየን ነው ማለት ነው፡፡ በመሰረቱ ሀገር በስራ እንጂ በሰልፍና በጩኸት አትለወጥም፣ አታድግምም፡፡ የውጭ ሀይሎች ተላላኪና መሳሪያ መሆን፤ የሀገርን ልማትና እድገት ለማጨናገፍ በፖለቲካ ሽፋን መንቀሳቀስ በሀገር ላይ የሚፈጸም ከባድ ወንጀል ነው፡፡ በሰማያዊው ፓርቲ ሰልፍ ላይ የታየው የሌሎች ተቃዋሚ ፓርቲዎች መሪዎችና አባላት ብቻ ሳይሆኑ በአብዛኛው ለአክራሪዎች ወግኖ የቆመው ኃይል ነው፡፡ይህም ሰማያዊው ፓርቲ አስቀድሞ ውስጥ ውስጡን የማስተባበር ስራ መስራቱን በገሀድ ያረጋግጣል፡፡ መካከለኛ እድሜ ላይ ያሉና አዛውንቶች ጭርሱንም በሰልፍ ላይ የሉም ማለት ይቻላል፡፡
የሰልፈኛው ቁጥር አናሳ ከመሆኑ አንጻር ያን ያህልም ግምት የሚሰጠው እንዳልሆነ በግልጽ የሚታወቅ ቢሆንም፣ «ለራስ ሲቆርሱ አያሳንሱ» ዓይነት ተረት ሆነና 100 ሺ ሰው ሰልፍ ወጥቷል ሲሉ የሰማያዊ ፓርቲ ኃላፊ ከእውነታው የተጣላ መግለጫ ለተለያዩ ሚዲያዎች ሰጡ፡፡ ኢትዮ ምሕዳር ጋዜጣም ይህንኑ በማስተጋባት ይሁን በራሱ ስሜት ተነሳስቶ እንደሆነ አይታወቅም በመጀመሪያ ገጹ ላይ «100 ሺ ሰዎች ሰልፍ ወጡ» ሲል ግነቱን በመድገም ዘገባ አቅርቧል፡፡ መልእክቱ አያሻማም፣ ለቀጣዩ ሰልፍ ሰዎች እንዲሰናዱ በኋላም ብዙ መቶ ሺዎች ወጡ ለማለት እንዲመች የተዘጋጀ የቅድመ ፕሮፖጋንዳ ስራ ወይም የቅስቀሳ ማስታወቂያ መሆኑ ነው፡፡
ሌሎቹም የውስጥና የውጭ ሚዲያዎች ከ1997 በኋላ የነበረው ፍርሃት ተሰበረ በሚል በመቶ ሺዎች ሰልፍ ወጡ፤ መንግስት በሶስት ወራት ለቀረቡለት ጥያቄዎች መልስ ካልሰጠ ተቃውሞውና ሰልፉ ተጠናክሮ ይቀጥላል፤ ተቃዋሚውም የበለጡ የተቃውሞ ሰልፎችን ለማድረግ እቅድ እያወጣ ነው፣ ተባብሮ እየሰራ ነው የሚሉ ዘገባዎችንም አንብበናል፡፡
ለዚሁም ተግባራዊነት አሜሪካና አውሮፓ ከሚገኙ አክራሪ ተቃዋሚ ሀይሎች ገንዘብ የማሰባሰብ ስራ እየተካሄደና ከወዲሁም ለመንቀሳቀስና ለማስተባበሪያ የሚሆን ገንዘብ በተለያዩ ሽፋኖች ወደ ሀገር ውስጥ እየገባ መሆኑን አንዳንድ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ በቀጣይም መሰል የተቃውሞ ሰልፎችንና የአደባባይ ስብሰባዎችን ለማደራጀት እንደሚንቀሳቀሱ እየገለጹ ይገኛሉ።
የአረቡ ዓለም ዓይነት አብዮት በመፍጠር በሁከትና በትርምስ መንግስትን በኃይል ለመጣል ይቻላል ብለውም ዕምነት ይዘዋል። ይህ ግን ኢ-ሕገመንግሥ ታዊና ሕገወጥ ከመሆኑም በላይ የሃገራችን ነባራዊ ሁኔታ ሊያስተናግደው የማይችል ከንቱ ምኞት ከመሆን የዘለለ አይሆንም።፡፡ እነሱ እንዳሰቡት ሕብረተሰቡ የስውር ሴራቸውና የአመጻቸው ተባባሪ ይሆናል ተብሎም ጭራሽ አይታሰብም። በዚህ ዓይነቱ ድርጊት ጀርባ በቀጥታና በተዘዋዋሪ የእነማን እጅ አለ? የነማንን ጥቅም ለማስከበርና ዓላማ ለማሳካት ነው ይህ ሁሉ እየታሰበ ያለው? ለዚህ ዓላማ መሳካት ሲባልስ በተለያየ መንገድ ከውጭ የሚገባ ስውር ድጋፍ የለም ወይ? የተለያዩ ክፍተቶች እንዲፈጠሩ በማድረግ የራሳቸውን ጥቅም ለማስከበር የሚራወጡ የተለያዩ የውጭና የውስጥ ኃይሎች የሉም ወይ? ወዘተ የሚሉትን ጥያቄዎች አንስቶ በሚገባ መፈተሽ ተገቢ ይሆናል። የመንግሥትን ጥብቅ ክትትልና ቁጥጥር በመፍራት ኢትዮጵያ ውስጥ ባሉ በመንግስትም ሆነ በግል የገንዘብ ተቋማት በኩል ግዙፍ ገንዘብ በቀጥታ አይልኩም፡፡ ሽብርተኞች በውጭው ዓለም እንደሚያደርጉት ሁሉ እነዚህም ጨዋታውን የሚያካሂዱትና ገንዘብ የሚያስገቡት ሕጋዊ ባልሆኑ የተለያዩ ስውር መንገዶች ነው፡፡
ይህ ሁሉ ደፋ ቀና በእርግጥ በዚህች አገር የተሻለ ለውጥ ለማምጣት ሳይሆን የሀገሪቷን ሰላም በማደፍረስ ወደ ሁካታና ትርምስ ማዕከልነት ለመለወጥ በዚህም ጥፋትና ውድመት መካከል በሚፈጠር የመርፌ ቀዳዳ በሚያህል ክፍተት ተሽሎክሉኮ በሕገወጥነትና በኃይል ሥልጣን መጨበጥ ብቻ ነው፡፡ ይህ የቀን ቅዥታቸው ግን በምንም መንገድ ዳር የሚደርስ አይሆንም፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለዚህ የኢትዮጵያ ጠላቶች ከጀርባ ሆነው በፋይናንስ በመርዳት ለሚያደርጉት ርብርብ ውስብስቡን ገጽታቸውን ስለሚረዳው ፈጽሞ አይንበረከክም፡፡
የታላቁን ሕዳሴ ግድብ ግንባታና ሌሎችን የተጀመሩ ፈጣን የልማት እንቅስቃሴዎችን ለመግታት የሚራወጡት በተቃዋሚነት ስም ያሉ ሰማያዊ ፓርቲን የመሳሰሉና ሌሎች የሃይማኖትና የፖለቲካ ጽንፈኞች እንቅስቃሴ በአንዳንድ የውጭ ሀይሎች ስለላና መረጃ እንዲሁም ቀጥተኛ የፋይናንስ ድጋፍ ሊታገዙ እንደሚችሉ መገመት ከእውነታው የራቀ አይሆንም። ይህን ለማለት የሚያስደፍረውም በአቋም ደረጃ እያራመዱት ያለውና በተግባርም እንተረጉመዋለን የሚሉት ሁሉ ያለው ተመሳሳይነት ነው። የሰማያዊ ፓርቲ፣የአንድነትም ሆነ የመድረክ ሽር ጉድ ለሰላም፣ለዕድገት፣ለፍትሕና ለዲሞክራሲ መስፈን ሳይሆን በአቋራጭ ራሳቸውን ለሥልጣን ለማብቃት የሚያደርጉት የህልም እሩጫ ነው።
ለዚህም ሕዝቡን ለማነሳሳት፣በዲሞክራሲና በሰብአዊ መብት ስም መነገድ፤የሕዝብ ስሜትን ይቀሰቅስልናል ብለው የሚያስቡትን የተዘጋና ፈጽሞ ተቀባይነት የሌለውን አጀንዳ ሁሉ ከተቀበረበት አውጥቶ የሌለ ሕይወት ለመስጠት አቧራ ማስነሳት፣ በአሸባሪነት ተጠርጥረው ጉዳያቸው በነጻ ፍርድ ቤት በመታየት ላይ ያሉ ሰዎችንና ቀደም ብሎም የፍርድ ውሳኔ የተላለፈባቸውን በተመለከተ ከፍርድ ቤት ይልቅ ራሳቸውን ፈራጅ አድርገው በመሰየም ይፈቱ ማለትና በዚህም አክራሪነትንና ጽንፈኝነትን መደገፍ ነው ስራየ ብለው የያዙት፡፡
ታላቅ የሆነ ሀገራዊ ጉዳይ እያለ ያንን ለማሰናከልና ለውጭ ሀይሎች መሳሪያ በመሆን ሕዝቡን ለመከፋፈል መሮጣቸው ማንነታቸውን ይበልጥ አጋልጦታል፡፡ ማንም በዚህ የሚዘናጋና የሚታለል አይኖርም፡፡ ጥሪያቸውም ሆነ ቅስቀሳቸው ተቀባይነት የለውም፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ፣ የአንድነትና የመድረክ ጥቁር ተግባራት ሀገሪቷን ወደ ጥፋት አቅጣጫ ለመውሰድ ያነጣጠረ እንጂ ለሕዝብ ጥቅምና ክብር ከማሰብ የመነጨ አይደለም፡፡ በዚህ ድርጊታቸው ግን የታሪክና የትውልድ ተጠያቂነትም እንደሚኖርባቸው ጠንቅቀው ሊገነዘቡት ይገባል፡፡