Monday, December 24, 2012

በህውሀት የብቸኝነት እዝ የሚመራው የኢትዮጵያ ሰራዊት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ከሚደረጉ ህዝባዊ ትግሎች ጎን እንዲሰለፍ ጥሪ ቀረበ


ኢሳት ዜና:-የኢትዮጵያ ህዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ የትግል አቅጣጫውንና የኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ባወጣው መግለጫ እንዳመለከተው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊትና የደህንነት ሀይሎች ለመንግስት ህዝብን የመጨቆኛ መሳሪያ መሆናቸውን አቁመው ከህዝብ ጎን እንዲቆሙ ጥሪውን አስተላልፎል::ታህሳስ ፲፭(አስራ አምስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ህውሀት ኢህአዴግ በህዝባችን ላይ የሚያደርሰው በደልና ግፍ ሊያበቃ ይገባል ያለው የሸንጎ መግለጫ በእስር ላይ ያሉት የፖለቲካና የህሊና እስረኞች ባስቸኮይ እንዲፈቱም መንግስትን አሳስቦል::
አፋኝ የሆኑ የሚዲያና የሽብርተኝነት ህጎች በሙሉ እንዲሰረዙ ያሳሰበው የኢትዮጵያ ህዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ የመንግስት ሚዲያዎች ለምርጫ ግዜ ብቻ ለፕሮፓጋንዳ ሲባል የሚሰጥ ሽርፍራፊ ሰአት ቆሞ በመደበኛነት የተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚሳተፉበት እንዲሆን ጥሪ አቅርበዋል\::
የዲፕሎማቲክ የበላይነት በአንድ ወይም በሁለት ድርጅት ትግል እንደማይገኝ ያመለከተው የሸንጎ መግለጫ ለዘለቄታ ዲፕሎማሲያዊ የበላይነት ለመብቃት ጠቃሚ ስትራቴጂዎችን በመቀየስ ከሌሎች ሀይሎች ጋር በጋራ ለመስራት ዝግጁ መሆኑን አመልክቶል::

የግንቦት7 ህዝባዊ ሐይል ከሌሎች ድርጅቶች ጋር በጋራ እየሰራ መሆኑን አስታወቀ




ኢሳት ዜና:-የድርጅቱ ቃል አቀባይ ታጋይ ዜና ጉታ ለኢሳት እንደገለጠው ከትግራይ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ ወይም ደሚት፣ ከኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር፣ ከኢትዮጵያ ህዝብ ፍትህና እኩልነት ግንባር፣ ከጋምቤላ ህዝብ ነጻነት ንቅናቄ፣ ከቤንሻንጉል ህዝብ ነጻነት ንቅናቄ እንዲሁም የአማራ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ከተባሉት ድርጅቶች ጋር በጥምረት ለመስራት አስፈላጊው ዝግጅት አጠናቋል።ታህሳስ ፲፭(አስራ አምስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ታጋይ ዜና ጉታ ህዝባዊ ሀይሉ በዶ/ር ብርሀኑ ነጋ ከሚመራው የግንቦት7 የፍትህ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ጋር ግንኙነት እንዳለው ጥያቄ ቢቀርብለትም አስተያየት ከመስጠት ተቆጥቧል።

ESAT EthiopiaTikuret Fez ralizm Tamagn Beyene Part 2

ሰበር ዜና – ማኅበረ ቅዱሳን ራሱንና የአባላቱን አቋም በመፃረር በፓትርያሪክ ምርጫው ለመሳተፍ ወሰነ


ሐራ ዘተዋሕዶ

  • ማኅበሩ ዲ/ን ዓባይነህ ካሴ ለአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ የሰጡትን አስተያየት አስተባብሏል
  • የማኅበሩ ምክትል ሰብሳቢ ከመንግሥት ለተመደቡት ባለሥልጣን እገዛ ትሰጣለች
  • ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በማኅበሩ ጥቂት አመራሮች አቋም ግራ ተጋብተዋል
  • የማኅበሩ የሰሜን አሜሪካ ማእከል ሰብሳቢ የአቋም ለውጡን በመቃወም ‹‹ውሳኔው አያስማማንም፤ የማስቀድመው ዕርቀ ሰላሙን ነው›› ብለዋል፡፡
‹‹ቤተ ክርስቲያናችንን ወደ አንድነት የሚያመጣ ዕርቀ ሰላም መፈጸም ከሃይማኖታዊ ሥነ ምግባር አንጻር፣ ለቤተ ክርስቲያን ደኅንነት ከማሰብ አንጻር፣ መንጋውን ከማነጽና ሐዋርያዊ
Uganda, Kampala Ethiopian Orthodox Church
Uganda, Kampala Ethiopian Orthodox Church
አገልግሎትን ከማቅናት አንጻር ለአባቶቻችን ግዴታ ይኾንባቸዋል፡፡ የሚፈለገው ዕርቀ ሰላም እውን እንዲሆንም ለእግዚአብሔር ፈቃድ፣ ለእውነት፣ ለኅሊና ምስክርነት መገዛት አግባብ ይሆናል›› – ይህ መልእክት በሐመር መጽሔት፣ 20 ዓመት ቁጥር 8፣ ታኅሣሥ 2005 ዓ.ም በወቅታዊ ጉዳይ ላይ የወጣ፣ በድረ ገጹም የተደገመ የማኅበረ ቅዱሳን አቋም ነው፡፡ ይህ የማኅበረ ቅዱሳን መልእክት‹‹ከምርጫው ይልቅ ዕርቀ ሰላሙ ይቅደም››ከሚለውና ማኅበሩ የበለጠ ከሚታወቅበት አቋሙ የመነጨ ነው፡፡
ማኅበረ ቅዱሳን በመልእክቱ ዕርቅ÷ ‹‹በቤተ መቅደሱ ዕለት ዕለት መሥዋዕት ለሚያቀርቡ፣ ብዙዎችን በጸጋ እግዚአብሔር ባዕለጸጋ ለሚያደርጉ፣ ምስጢራትንም ሁሉ ለሚፈጽሙ፣ የሃይማኖትና የሥነ ምግባር ምልክት ለሆኑ ከሁለቱም ወገን ያሉ ብፁዐን አባቶች የሚያስተምሩት ብቻ ሳይሆን ዘወትር እንዲኖሩት የሚጠበቅ ክርስቲያናዊ ሕይወት›› መኾኑን መክሮ ነበር፡፡ መምከር ብቻ ሳይሆን÷ ቤተ ክርስቲያን ለኻያ ዓመታት ያሳለፈቻቸው አሳዘኝ ኹኔታዎች እንዳይቀጥሉ ዛሬ ላይ መደረግ የሚገባው ሁሉ መደረግ ይኖርበታል ብሎ እንደሚያምን፣ ለዚህም እንደሚሠራ አቋሙን አስታውቆ ነበር፡፡
ዛሬ፣ ታኅሣሥ 12 ቀን 2005 ዓ.ም ከቀትር በኋላ ከመንበረ ፓትርያሪኩ የተሰማው ዜና ግን ማኅበሩ በቤተ ክርስቲያን ሰላምና አንድነት ጉዳይ ማድረግ ከሚችለው አስተዋፅኦ አንጻር በውጭም በውስጥም፣ በቅርብም በሩቅም ተስፋ ለሚያደርጉት ወገኖች ሁሉ አንገት የሚያስደፋ ነው፡፡ የማኅበሩ ጥቂት አመራሮች በወሰኑት ውሳኔ ማኅበሩ ‹‹ቅድሚያ ለዕርቀ ሰላሙ›› ሲለው የነበረው መፈክር ‹‹ቅድሚያ ለምርጫው›› ወደሚለው ተለውጧል!!
የማኅበሩ ሥራ አመራር ጉባኤ አባል የኾነውና በነሐሴው የማኅበሩ 10 ጠቅላላ ጉባኤ ላይ በአወዛጋቢ አኳኋን የተመረጠው አቶ ባያብል ሙላቴ የአስመራጭ ኮሚቴው አባልነቱን የተቀበለ ሲኾን ዛሬ በተሰማው የማኅበሩ የአቋም ለውጥ ደግሞ የፓትርያሪክ ምርጫ ሂደቱን እንድትከታተል የማኅበሩ ምክትል ሰብሳቢ ወ/ሪት ዳግማዊት ኀይሌ መመደቧ ተነግሯል፡፡ አቶ ባያብል ሙላቴ ከሲኖዶሱ በተመደቡ ሰባት ሊቃነ ጳጳሳት አማካይነት ተቋቁሞ ያለበቂ ትችትና ውይይት በቀጥታ በጸደቀው 13 አባላት ባሉት አስመራጭ ኮሚቴ ውስጥ አንዱ አባል መኾ ናቸው ቢታወቅም ማኅበሩን ይወክላሉ በሚል የተመረጡበት መንገድ ግን ለብዙዎች ግልጽ አይደለም፡፡
የምክትል ሰብሳቢዋ ወ/ሪት ዳግማዊት የዛሬው ምደባ የአቶ ባያብል በአስመራጭ ኮሚቴ መካተት በማኅበሩ ላይ የፈጠረው አጣብቂኝ አስተዋፅኦ ሊያደርግ እንደሚችል የሚስማሙ ተቺዎች÷ ከመንግሥት ከፍተኛ አካላት ጋራ በዕርቀ ሰላሙና በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪክ አቡነ መርቆሬዎስ አመላለስ መካከል ስለመለየት እንዲሁም ስለ ተተኪ ፓትርያሪክ ምርጫ በተደጋጋሚ የተደረገው ውይይት ቀጥተኛ ጫና ሳያሳድር እንዳልቀረ ይናገራሉ፡፡ ዕርቀ ሰላሙ ዕንቅፋት የሚፈጥሩ ቀኖናዊ ጉዳዮችን ከግምት በማስገባት፣ ተቀባይነት የሌላቸውን ቅደመ ኹኔታዎች በማስወገድ መፈጸም እንደሚገባው የሚገልጸው ማኅበሩ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ወደ መንበር ይመለሱ የሚለውን በመቃወም የስድስተኛው ፓትርያሪክ ምርጫ መፈጸም ይኖርበታል ብሎ እንደሚያምን ተመልክቷል፡፡
ይኸው የማኅበሩ አቋም በተለይም የማኅበሩ ኤዲቶሪያል ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ የኾኑት ዲ/ን ዓባይነህ ካሴ ለአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ የአማርኛ ቋንቋ አገልግሎት በወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን የሰላም ጉዳይ ላይ አስተያየታቸውን ከሰጡ ወዲህ ተግዳሮት እንደገጠመው ይነገራል፡፡ ዲ/ን ዓባይነህ በማኅበሩ ያላቸውን ሓላፊነት ጠቅሰው ሲያበቁ÷ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስን ወደ መንበር መመለስ የተጣሰው ቀኖና የሚቃናበት አንድ አማራጭ መኾኑን ማስቀመጣቸው፣ ቅድሚያ ለዕርቀ ሰላሙ በማለት አሰምቶ የሚጮኸው በአራቱም ማእዝናት የሚገኝ ምእመን ድምፅ ሊደመጥ እንደሚገባው ማሳሰባቸው፤ ከማንም ተጽዕኖ ይመጣል ብሎ ሳይፈራ በመግባባት፣ መወያየት፣ መንቀሳቀስና መነጋገር እንደሚያስፈልገው መጠቆማቸው፤ የሁለቱ ወገኖች የሰላም ልኡካን አብረው መጸለያቸውና መቀደሳቸው ‹‹ታላቅ ርምጃ›› መኾኑን መናገራቸው የማኅበሩን የቀደመ አቋም የለወጡትን ጥቂት አመራሮች አለማስደሰቱ ተገልጧል፡፡
ይህን በተመለከተ የማኅበሩ አራት አመራሮች በትላንትናው ዕለት ምሽት ዲ/ን ዓባይነህን ያነጋገሩ ሲኾን በዛሬው ዕለት ማምሻውን ደግሞ ዲ/ን ዓባይነህ ለቪ.ኦ.ኤ የሰጡት ቃለ ምልልስ ማኅበሩን እንደማይወክልና የግላቸው መኾኑን በድረ ገጹ አስታውቋል፡፡ ዲ/ን ዓባይነህ በሬዲዮው ቃለ ምልልሳቸው የሰጡት አስተያየት የማኅበሩ አመራሮች ከመንግሥት ከፍተኛ አካላት ባደረጉት ውይይት ካስቀመጡት አቋምና በየጊዜው ለሊቃነ ጳጳሳቱ ከሚሰጡት ማብራሪያ ጋራ ‹‹የተጋጨ ነው፤ አባቶችን የሚከፋፍል ነው›› መባሉ የማኅበሩን ጥቂት አመራሮች ዛሬ የተሰማውን ዐይነት ግልጽ ነገር ግን በታሪክ አሳዛኝ የኾነ አካሄድ ውስጥ እንዲገቡ እንዳስገደዳቸው ተተችቷል፡፡ ወዲያውም ደግሞ ‹‹ርምጃ ወስደን እናሳውቃችኋለን›› ላሏቸው እንደ ብፁዕ አቡነ ጎርጎሬዎስ ላሉት ሊቃነ ጳጳሳት የተግባር ምላሽ መኾኑ ተመልክቷል፡፡
ወ/ሪት ዳግማዊት በተመደበችበት ሓላፊነት ‹‹የፓትርያሪክ ምርጫውን ሰላማዊ ለማድረግ›› በሚል ከፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር የሃይማኖት ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ለተመደቡት አቶ ትእዛዙ ደሳለኝ መረጃዎች በመስጠትና ከአባቶች ጋራ በማቀራረብ እንደምትረዳ ተጠቁሟል፡፡ በተመሳሳይ አኳኋን የማኅበሩ ጽ/ቤት ሓላፊዎች የማኅበሩ የዋናው ማእከል ጽ/ቤት ልዩ ልዩ ክፍሎች÷ ማኅበሩ በምርጫው ላይ በማተኮር ለሚሠራው ሥራ እንዲዘጋጁ መመሪያና ማሳሰቢያ ሲሰጡ መዋላቸው ተዘግቧል፡፡
ይኹንና ውሳኔው የማኅበሩ ከፍተኛ አመራር ሰሞኑን ባካሄደው ስብሰባ ዕርቀ ሰላሙ ቅድሚያ እንዲሰጠውና በትኩረት እንዲሠራበት በሙሉ ድምፅ ሊባል በሚችል መልኩ ያሳለፈውን መመሪያ የሚፃረር መኾኑን የገለጹ ወገኖች በአቋም ለውጡ ‹‹ራሱንና ለረጅም ጊዜ በጋራ ሲሠራበት የነበረውን የአባላቱን አቋም ተፃሯል›› ማለታቸው ተሰምቷል፡፡ የቀድሞው የማኅበሩ ሰብሳቢ ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ሥዩም÷ ዕርቅ ሳይፈጸም ምንም ዐይነት እንቀስቃሴ እንዳይደረግ አበው መነኰሳቱ ለአባቶች እንዲመክሩና ኹኔታውንም በጸሎት እንዲያስቡ የተማፀኑት በትላንትናው ዕለት ምሽት አምስት ብፁዓን አባቶች በተገኙበት በተዘጋውና ለስድስት ቀናት የቆየው 70 የገዳማት አበምኔቶች ከ61 ገዳማት በተገኙበት ዐውደ ጉባኤ እንደነበር ተወስቷል፡፡
የማኅበሩ የሰሜን አሜሪካ ማእከል ሰብሳቢ የኾኑት ቀሲስ በላቸው ወርቁ ከዋናው ጽ/ቤት ሓላፊዎች ጋራ በስልክ አድርገውታል በተባለ ውይይት÷ ‹‹የተወሰነው ውሳኔ ፈጽሞ አያስማማንም፤ እኛ የምናስቀድመው ዕርቀ ሰላሙን ነው፤ ባለሁበት ቤተ ክርስቲያን በምሰጠው አገልግሎት ከዚህ የማኅበሩ አቋም እለያለኹ›› በሚል ተቃውሟቸውን መግለጻቸው ተገልጧል፡፡
ለሁለት ዐሥርት ዓመታት መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊና ልማታዊ አገልግሎት በመፈጸም የትውልድ ግዴታውን እየተወጣ የሚገኘውን የማኅበረ ቅዱሳንን ክፉ መስማትም ማየትም አንሻም፡፡ ነገር ግን÷ ከቤተ ክርስቲያን አንድነትና ሰላም የሚቀድም ነገር ደግሞ የለም፡፡ ማኅበሩ ለቤተ ክርስቲያን ሰላምና አንድነት እስከቆመ ድረስ ሁሉም ከጎኑ ይቆማል፤ አሰላለፉ፣ ስልቱ ይህን ሲቃረን ደግሞ ብቻውን ይቀራል፡፡
የቤተ ክርስቲያንን ሰላምና አንድነት እንደሚያረጋግጥ በዓለም ዙሪያ በሚገኙ አገልጋዮችና ምእመናን ታምኖበት እየተደከመበት የሚገኘው ‹‹የዕርቀ ሰላም ይቅደም›› ጥያቄ ወደ አዲስ ምዕራፍ ሊሸጋገር ባለበት ዋዜማ ማኅበሩ የወሰደው አቋም ክፉኛ ያሳስበናል፡፡ ማኅበሩ በርግጥም ለቤተ ክርስቲያን ሰላምና አንድነት ድምፁን ከፍ አድርጎ ለማሰማት ከተዘጋጀው ምእመን ጋራ ለመሰለፍ የተዘጋጁ ብዙኀን አመራሩና አባላቱ ማኅበር ከኾነ ጊዜው ከማለፉ በፊት የዛሬውን አቋሙን ያጢን፣ ይመርምር እንላለን ! ! !

Sunday, December 23, 2012

ግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል ተመሰረተ (ግንቦት 7 ዜና)



News, Ginbot 7 Movement for Justice, Freedom and Democracy.www.ginbot7pf.org በሚል ድረ ገጽ ላይ የወጣው መግለጫ እንደሚያመለክተው የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል የሚባል ድርጅት መመስረቱ ተገለጸ ።  መግለጫውን ያወጣው የግንቦት ሰባት ህዝባዊ ሃይል እንዳብራራው ታህሳስ 11 ቀን 2012 ዓም ” የወያኔን ዘረኛና አምባገነን አገዛዝ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጫንቃ ላይ በትጥቅ ትግል ለማስወገድ “የግንቦት7 ሕዝባዊ ኃይል” የሚል ስያሜ የሰጠነውን፣ በሃገር ወዳድና ለህዝብ ተቆርቋሪ በሆኑ ወጣቶች፣ ምሁራንና ዜጎች የተሞላውን ድርጅት መመሥረታችን በዛሬው እለት ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ በይፋ እናበስራልን” ብሎአል።
“የሕዝብ ሉዓላዊ የሥልጣን ባለቤትነት የተረጋገጠባት፤ የዜጎች መብቶች፣ ሃገራዊ አንድነት፣ ደህንነትና ጥቅም የተከበሩባት ጠንካራና ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ እውን ሆኖ የማየትን ራዕይ የሰነቀ ድርጅት መሆኑን” የገለጸው ህዝባዊ ሀይሉ፣ መንግስትን በኃይል የማስወገድ፤ ሰላማዊና ዲሞክራሲ የሥልጣን ሽግግር በሃገሪቱ እንዲኖር የማስቻል እና ከማንኛዉም የፓለቲካ ድርጅት ጋር ያልወገኑ ነፃ፣ ጠንካራና ብቃት ያላቸው ህገ-መንግሥታዊ የመከላከያ፣ የፓሊስና የደህንነት ተቋማት እንዲኖሩ አስተዋጽዖ የማድረግ ተልዕኮ” ይዞ መነሳቱን ገልጿል።
ህዝባዊ ሀይሉ “በሃገራችን በወያኔ አምባገነናዊ እብሪት ያልታፈነ፣ ያልተዋረደና ያልተዘረፈ የሃገሪቱ ዜጋ እንደማይገኝ ገልጾ፣ ሹማምንቱ በሃብት ላይ ሃብት፤ በድሎት ላይ ድሎት ሲጨምሩ፣ የአብዛኛው ኢትዮጵያዊ እጣ ፈንታ ግን መፈናቀል፣ መሰደድ፣ መንገላታት፣ መታሰር፣ መደብደብና መገደል ሆኗል” ብሎአል። “የወያኔ  የአመጽ እብሪት በሕዝባዊ አመጽ የሚተነፍስበት ሁኔታ  እስካልመጣ ድረስ፣ ወያኔ መብታቸውን ከመጠየቅ ውጭ ምንም እንከን የሌለባቸውን ንጹሃን ዜጎች ከማሰር፣ ሰቆቃ ከመፈጸም፣ ከመግደል ከማሳደድና  ከማፈናቀል” እንደማይቦዝን ህዝባዊ ሐይሉ ገልጿል።
የግንቦት7 ህዝባዊ ሀይል ” ዜጎች በሽብርተኛነት እየተከሰሱ በእድሜ ልክ እስራት ሲቀጡና ሰቆቃ ሲፈፀምባቸው የታዘባችሁ ወጣቶች፤ ለሃይማኖት እኩልነት በመታገላቸው በእስር ላይ እየማቀቁ፣ እየተገረፉና እየተሰቃዩ ያሉ የሙስሊም ምዕመናን ተወካዮች ጉዳይ የሚያሳስባችሁ ወገኖች፤ በቤተክህነትና በክርስትና ተቋማት ላይ እየተፈፀመ ያለው ደባ የሚያንገበግባችሁ ፤ ለወያኔዎችና ሸሪኮቻቸው እድገትና ምቾት ሲባል ከይዞታችሁ የተፈናቀላችሁ፤ ገቢን ሳይሆን ወገንተኛነትን መስፈረት ባደረገ መመዘኛ ከአቅም በላይ የሆነ የወያኔ ግብር፣ ታክስና መዋጮ የተማረራችሁ ነጋዴዎች፤ ማኅበራችሁ በወያኔ ፈርሶ ወይም ተጠልፎ የጋራ ድምፃችሁን የምታሰሙበት፣ ከቀጣሪያችሁ ከወያኔ  ጋር ፍትሃዊ የጉልበታችሁን ዋጋ ክፍያ መደራደሪያ ያጣችሁ ላብአደሮች፣ መምህራን፣ የሲቪል ሰርቪስ ሠራተኞች፤ ምንም አይነት የአካዳሚ ነጻነት በሌለበት ሁኔታ ጥራቱን ያልጠበቀ ትምህርት እንድትከታተሉ የተፈረደባችሁ፣ ትምህርታችሁን ጨርሳችሁ ከየኮሌጁና ከየዩንቨርስቲው ስትመረቁ እጣችሁ ድንጋይ ማንጠፍ የሆነው ወጣት ተማሪዎች” ትግሉን ተቀላቀሉ ሲል ጥሪ አቅርቧል።
ህዝባዊ ሀይሉ “አደገኛ በረሃዎችንና ባህሮችን በማቋረጥ ለመሰደድ ልባችሁ እየከጀለ ላሉ ወጣቶች፣ በአረብ ሃገራት ለባርነት ስራ ተሽጠው እጣቸው ተገዶ  መደፈር፣ በፈላው ወሃ መቀቀል፣ መደብደብ፣ መዋረድና ከፎቅ ላይ እየተወረሩ ክቡር ህይወትን ማጣት ለሆነው ሴቶች፣  ለሃገር አንድነትና ክብር መሰለፍ እንደ ወንጀል ተቆጥሮባቸው እንደ ባዕድ ጦር የተበተኑና የተገፉ በመከላከያ ሰራዊት ውስጥ በሚታየው ዘረኛነት እየተቃጠሉ፣ በሕዝብ ላይ ዝመቱ በተባሉ ቁጥር ከህሊናቸው  ጋር መዳማት የመረራችው የኢትዮጵያ ወታደሮች እና በድህነት አስገዳጅነት፣ እንዲሁም በሌሎችም ማስፈራሪያዎችና ጫናዎች የወያኔ/ኢህአዴግ ድርጅቶች አባል የሆኑ ወገኖች በሙሉ” ጥሪውን ሰምተው ትግሉን እንዲቀላቀሉ ጠይቋል።
በ http://www.ginbot7pf.org ድረገጽ ላይ የወጣው ዜና እንደሚያመለክተው ህዝባዊ ሀይሉ ራሱን በትጥቅና በሰው ሀይል አደራጅቷል።

Wild celebrations as news of the formation of a crack guerrilla group reach South Africa!


The Horn Times Breaking News, 21 December 2012
by Getahune Bekele, Johannesburg
“Tekebresh yenorshiw babatochachin dem,”
Enat Ethiopia yedeferesh yewdem,”

The patriotic song made famous by the incomparable Ethiopian singer Shambel Belayneh was on everyone’s lips on
GPF, Ginbot 7 popular Force fighters on the move.
GPF, Ginbot 7 popular Force fighters on the move…
Saturday morning 21 December 2012, when the Horn Times visited the bustling GP street in central Johannesburg where Ethiopian refugees usually gather in large numbers.
“President Jacob Zuma, it is time to return the favor, help our freedom fighters…” an excited Ethiopian refugee shouted at a passing police van while his friends whistle and scream “freedom! Freedom!”
“The day 90 million Ethiopians patiently waited for has finally arrived.
And the long walk to freedom begins now. Begging for freedom from a homicide maniac has come to a grinding halt. This is the way to go if we want to break the bondage of slavery.” Henock Alemayehu, 24, a college student in the city of Pretoria told the Horn Times, smiling ear to ear.
As the announcement of the formation of the guerrilla group spread throughout South Africa like wildfires, GPF was also showered with congratulatory messages and some freedom loving refugees even pledged financial assistance.
Here in South Africa, many exiles believe the announcement would trigger a mass defection from non-Tigre members of the brutal TPLF army and the regime would collapse sooner than expected.
The Ethiopian community association in South Africa spokes person also lauded the formation of the GPF as a milestone in the struggle against the rapacious minority junta and sent out his message of congratulations to Ginbot-7 opposition party leaders.
“The announcement of the formation of Ginbot 7 Popular Force, GPF, is like sweet melody to the ears of millions of Ethiopians. Attempting to talk peace with fascist warlords for 21 years had proved a total waste of time. It is time to talk to them with the only language they understand.” The spokesperson said.
“Deadly inter tribal clashes; hunger and disease are still blighting our country .Arbitrary arrest, torture and extrajudicial killings are perfectly legal. While the junta receives billions of dollars in foreign aid, material poverty is driving thousands out of the country. Ethiopia is nothing but the world’s biggest open air prison. To end all this, Ethiopia doesn’t need myopic political parties, we need crack guerrilla groups and GPF is the answer. It will carry the hopes and aspirations of 90 million Ethiopians.” The spokesman added.
Furthermore, a military analyst from Addis Ababa- Ethiopia told the Horn Times that if GPF fighters hit any area in the vast nation and hold on to a village or a town for few days, the brutally oppressed Ethiopians will rise against the junta.
“Look, in the TPLF army one platoon has 3 ethnic Tigre commanders and one Tigre political commissar. In one squad (9 solders) there is one Tigre commander and two gujjiles who are spying and watching the performances of contracted non- Tigre solders. That is why am saying if GPF fighters score even a miner victory, these unhappy solders will turn their guns on their commanders.” He explains.
In additional news, concerned Ethiopians in South Africa have called on Ethiopatriot website to stop demonizing respected opposition party leaders such as Dr Berhanu Nega and Andargachew Tsige.
“Patriots doesn’t call fellow patriots ‘traitors’, we know some great Ethiopians associated with the Ethiopatriot group. Let’s not fragment ourselves. Let’s slain the evil behemoth in Aratkilo together. Let’s rally around GPF.” The Ethiopians said.

Ethiopia 2012: Human Rights and Government Wrongs


by Alemayehu G. Mariam,

Another Groundhog Year

Ethiopia 2012: Human Rights and Government Wrongs
It was a repetition of 2007, 2006, 2005, 2004… Everyday millions of Ethiopians woke up only to find themselves trapped in a time loop where their lives replayed like a broken record. Each “new” day is the same as the one before it: Repression, intimidation, corruption, incarceration, deception, brutalization and human rights violation… They have no idea how to get out of this awful cycle of misery, agony, despair and tribulation. So, they pray and pray and pray and pray… for deliverance from Evil!
It is December 2012. Are Ethiopians better off today than they were in 2008, 2009, 2010, 2011? 
Does bread (teff) cost more today than it did in 2008…, a year ago? Cooking oil, produce, basic staples, beef, poultry, housing, water, electricity, household fuel, gasoline…?
Are there more poor people in Ethiopia today than there were in 2008? More hunger, homelessness, unemployment, less health care, fewer educational opportunities for young people?
Is there more corruption and secrecy and less transparency and accountability in December 2012 than in December 2008?
Are elections more free and fair in 2012 than in 2008?
Are there more political prisoners today than in 2008?
Is there less press freedom and are more journalists in prison today than in 2008?
Is Ethiopia more dependent on international handouts for its daily bread today than it was in 2008?
Is there more environmental pollution, habitat destruction, forced human displacement and land grabbing in Ethiopia today than 2008?
Is Ethiopia today still at the very bottom of the U.N. Human Development Index?