Tuesday, November 27, 2012

በኢትዮጵያ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ጎዳና ተዳዳሪዎች አሉ


ኢሳት ዜና:-በአዲስ አበባ ከተማ ከአንድ መቶ ሺህ በላይ ጎዳና ተዳዳሪዎች መኖራቸውን የተባበሩት መንግስታት የህጻናት መርጃ ድርጅት ጥናት አመለከተ።
የኢትዮጵያ መንግስት ማእከላዊ ስታትስቲክ መስሪያ ቤት ደግሞ በአዲስ አበባ ያሉት ጎዳና ተዳዳሪዎች 60 000 ብቻ ናቸው የሚል መረጃ አሰራጭቷል።
የተባበሩት መንግስታት የአለም አቀፉ የህጻናት መርጃ ድርጅት ዩኒሴፍ እንዳመለከተው በኢትዩኦጵያ በአጠቃላይ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ጎዳና ተዳዳሪዎች ሲኖሩ ከዚህ ውስጥ አንድ መቶ ሺዎቹ በርዕሰ መዲናዋ አዲስ አበባ ይገኛሉ።
የኢትዮጵያ ማእከላዊ ስታትስቲክ መስሪያ ቤት በአጠቃላይ በኢትዮጵያ የሚገኙ ጎዳና ተዳዳሪዎች 150 000 ብቻ ናቸው ሲል አመልክቷል። ከዚህ ውስጥ አንድ ሶስተኛው ወይንም 60 000 ሺዎቹ በአዲስ አበባ ይገኛሉ ብሎል።
አለም አቀፍ ተቋማት የሚያወጡትን መረጃ የኢትዮጵያ መንግስት የማይቀበልባቸው አጋጣሚዎች የበዙ ናቸው። የአለም ጤና ድርጅት ከአለም ባንክ ጋር በጋራ ባወጡት ሪፖርት ከኢትዮጵያ ህዝብ ውስጥ 17.6 በመቶ ወይም 14 ሚሊዮን ህዝብ የአካል ጉዳተኛ ነው ማለታቸው ሲታወስ አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀ/ማሪያም ደሳለኝ ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ አልተጠናም በማለት መቃወማቸው ተዘግቧል።

    Monday, November 26, 2012

    ስዊድን ኢትዮጵውያውያን ጥገኝነት ጠያቂ ጋዜጠኞችን ወደ አገራቸው እንዳትልክ የስዊድን ጋዜጠኛ ጠየቀ


    ኢሳት ዜና:-ከአመት በላይ በቃሊቲ እስር ቤት ታስሮ የተፈታው ዮሃን ፐርሹን ይህን ያስገነዘበው ትናንት ባለፈው ሳምንት በስቶክሆልም ስዊድን ከተማ በሚካሄደው ዓመታዊው ታላቁ የስዊድሽ ጋዜጠኞች ሽልማት ስነስርዓት ላይ ሲሆን በዚሁ ወቅት እሱና ባልደረባው  ማርቲን ሺብዬ ከእስር ተፈተው በነጻነት እንደልባቸው ለመንቀሳቀስ ቢችሉም በአሁን ሰዓት በቃሊቲ እና በሌሎች እስር ቤቶች በመማቀቅ ላይ የሚገኙት ኢትዮጵያውያን የህሊና እስረኞች ጉዳይ እጅግ እንደሚያሳስባቸው ተናግሯል።
    በቃሊቲ ታስረው የሚገኙ ጋዜጠኞች ወንጀላቸው መንግስትን የሚተቹ ጽሁፎችን በመጻፋቸው ብቻ ነው፡እነዚህ የህሊና እስረኞች በአሸባሪነት ተከሰው እስከ 20ዓመት የሚደርስ እስራት የተፈረደባቸው ሲሆን በዚህም የተነሳ ኢትዮጵያ ጋዜጠኞቿን እንዲሰደዱ በማድረግ በግንባርቀደምትነት ተጠቃሽ ነች።
    በስደት ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የእኛን እስር በተመለከተ በአማርኛ በመጻፍ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖረው ህብረተሰብ ግንዛቤ እንዲያገኝ ያደረጉት ጥረት መቼም አንዘነጋውም።  ስዊድን ጋዜጠኞችን ወደ ቃሊቲ ከመላክ እንድትቆጠብ እጠይቃለሁ በማለት በሽልማት ስነስርዓቱ ላይ ለተገኙት ጋዜጠኞችና የሚዲያ ተወካዮች የችግሩን አሳሳቢነት አመልከቷል።
    ከሽልማቱ ስነስርዓቱ ማብቂያ በኋላ በሰጠው ቃለምልልስ እሱና ባልደረባው ይግባኝ ያልጠየቁት በኢትዮጵያ ባለው የፍትህ ስርዓት እምነት ስሌላቸው መሆኑን በመጥቀስ የእነእስክንድር ነጋን ይግባኝ ለማየት ከተቀጠረው ችሎት ምንም የተለየ ነገር እንደማይጠብቅ ገልጿል።
    ባልደረባው ማርቲን ሺብዬ በበኩሉ በሰጠው አስተያየት በእለቱ ቪየና ኦስትሪያ ዩኔስኮ በግጭት ክልሎች የሚገኙ ጋዜጠኞች ደህንነት እንዴት መከላከል እንደሚቻል ለመወያየት ባዘጋጀው ስብሰባ ላይ በመገኘት ኢትዮጵያ ውስጥ ለ14 ወራት በታሰሩበት ወቅት ስላሳለፉት ስቃይ እና መከራ እንዲሁም በውሸት ማስረጃ ስለተከሰሱበት የፍርድ ሂደት ለተሰብሳቢዎቹ ማስረዳቱንና የስብሰባው ተሳታፊዎች በሁኔታው እጅግ መገረማቸውንና ማዘናቸውን ገልጿል።
    አብዛኛው ህብረተሰብ እኔ እና ዮሃን ከተፈታን በኋላ በኢትዮጵያ ያለው ችግር እንደተቃለለ ይገምታል ነገርግን አንድ መረሳት የሌለበት ጉዳይ የጸረሽብርተኝነት ህጉ አሁንም በስራ ላይ ሲሆን በሱም የተነሳ ብዙ ጋዜጠኞች በእስር ላይ በመማቀቅ ላይ ይገኛሉ።
    በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ የሚካሄደው የሰብዓዊ መብት ጥሰት እየተባባሰ ነው። ከዚህም በመቀጠል እሱና ማርቲን ቃሊቲ እስር ቤት ለሚገኙ ጓደኞቻቸው የገቡትን ቃልኪዳን በመጠበቅ በተገኘው አጋጣሚ ዓለምዓቀፉ ህብረተሰብ በኢትዮጵያ ላይ ጫና በማድረግ እነዚህ የህሊና እስረኞች እንዲፈቱ የሚያደርጉትን ትግል እንደሚያጠናክሩና በመጽሃፍ መልክ የሚታተተመው የእስርቤት ቆይታቸው በአማርኛ ተተርጉሞ ለኢትዮጵያውያን በነጻ እንዲያነቡት የሚቻላቸውን ሁሉ እንደሚያደርጉ አስታውቋል በማለት ቴውድሮስ አረጋ ከስዊድን ዘግቧል።

    Sunday, November 25, 2012

    የሱዛን ራይስ ሸፍጥ በቤንጋዚው ጥቃት ላይ!


    ፕሮፌሰር  ዓለማየሁ  ገብረማርያም 
    በሴፕቴምበር 2 2012 የአሜሪካዋ አምባሳደር በተባበሩት መንግስታት: ሱዛን ራይስ በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የቀብር ስርአት ላይ ስሜታዊ ሆና የሚያቅለሸልሽ ቃላት ያዘለ ንግግር አነብንባ ነበር፡፡ መለስን፤ ‹‹የማይደክምና ራሱን የማይወድ››በአጠቃላይ እሱነቱ ለስራውና ለቤተሰቡ የሆነ ብላዋለች፡፡ ‹‹ጠንካራ፤ በእምነቱ የጸና እና በእርግጥም ለጂሎችና ለደደቦች  እሱ እንደሚጠራቸው ትእግስቱ ትንሽ ነበር፡፡ ሱዛን ራይስ ይህን ቅጥ ያጣና ከአንድ አሜሪካን ከሚያህል ሃገር ወኪል ጨርሶ ሊሰማ የማይገባ ያልተገራ ንግግር ስታደርግ ጅልና ደደብ የሚለውን ቃል በድፍረትና በአጥንኦት የለጠፈችው በኢትዮጵያዊያን ነጻ ጋዜጠኞች፤የተቃዋሚ መሪዎች፤ተሟጋቾች፤የፖለቲካ እስረኞች፤የሲቪል ማሕበረ ሰብ መሪዎች፤እና የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ላይ ነው፡፡ የንግግሯን ቪዲዮ በመመልከት  ሴትዮዋ ይህን ንግግር የመለስን ተቃዋሚዎች በመጨረሻ ጡጫ  ደረታቸዉን ብላ ለመለስ የአስከሬን መሸኛ አድርጋ ማቅረቧ እንደነበር ያስታውቃል፡፡
    Susan Rice, the U.S. Ambassador to the U.N. Addis Ababa speech, Alemayehu G. Mariam
    ‹‹ አንድ አይነት ላባ ያላቸው ወፎች አብረው ይከንፋሉ›› ይባባል፡፡ ራይስ እንደ መለስ ሁሉ ተቃዋሚዎቿንና ሃሳቧን የማይጋሯትን ትሳደባለች ታንቋሽሻለች፡፡ በስቴት ዲፓርትመንት አካባቢ የሚያውቋት በዘለፋ በቁጣና በማስፈራራት አነጋገራዎ ነው፡፡ በዚህም አጉል ደንፊ ተብላ ትታወቃለች፡፡ አለያም በጣም በሚያውቋት ዘንድ ‹‹የቻይና መደብር በሬ›› (አተራማሽ ወይም በጥባጭ ማለት ነው) ይሏታል፡፡ በስብሰባዎች ላይ በቃላት ርችት፤በአፈነበልባል፤በጣት ቀሳሪነት ራይስ ትታወቃለች፡፡ በአንድ ወቅት በአሜሪካን ዲፕሎማቶች ዋና ታዋቂ በነበሩት ሪቻርድ ሆል ብሩክ ላይ የበላዮች ስቴት ዲፓርትመንት አባላት ስብሰባ ላይ በአሜሪካንና በሌላውም ዓለም በሳቸው ደረጃ ካሉ ሰዎች የማይጠበቀውንና ጸያፍ ተብሎ የሚጠራውን ድርጊት በአደባባይ የመሃል ጣታቸውን ቀስረውባቸዋል ይባላል፡፡

    በማርች 2012 የፈረንሳዩ የተባበሩት መንግስታት አምባሳደር ለራይስ እንደምክር የአውሮፓ ዩኒየን አሜሪካ ደገፈም አልደገፈም የበረራ ክልከላ ዞን ከተባበሩት መንግስታት የደህንነት ካውንስል ይፈልጋል በማለት ላቀረቡላት ሃሳብ ራይስ ለአምባሳደሩ ወሽመጥ በሚቆርጥ አነጋገር ‹‹መቼም ወደ አዛባ ጦርነታችሁ እንደማትጎትቱን አምናለሁ›› በማለት ከያዘችው ስልጣንና ከፈረንሳይ አቻዋ ጋር ሊደረግ በማይገባ የጋጠ ወጥ አባባል መልሳላቸዋል፡፡ በኋላ ግን ይህ ያጥላላችው ሃሳብ አመርቂ ውጤት በማስገኘቱ የሃሰቡ አፍላቂ በመምሰል ምስጋናውን ጠቅላ ለራሷ ለማድረግ በመዘየድ ‹‹ከማሰብና ከማቀድ ባለፈ የበረራ ክልከላውን ዞን በማጠናከር ልናተኩርበትና ልንተገብረውም አስፈላጊነቱ ወሳኝ ነው፡፡ የምድሩ ፍልሚያ ብዙም ስላላዋጣና ሲቪል ማህበረሰቡንም ከአደጋው ለመጠበቅ አዋጪው ይሄው ነውና›› በማለት ቀድማ ያጣጣለችውንና የፈረንሳዩን አቻዋን የሰደበችበትን ሃሳብ መልሳ በራሷ አፍላቂነት የተገኘ ለማስመሰል ጥራበታለች፡፡ ባለፈው ጁላይ ቻይናና ሩስያ ስለዓየር ለውጥ የቀረበውን ሂደት በተቃወሙበት ወቅት ራይስ ጉደኛዋ እዚህም ላይ ‹‹እርባና ቢስ›› ‹‹ሃሳበ ቢስ›› በማለት በማጣጣል ‹‹ የተግባር ውድቀት›› በማለት ኮንናቸዋለች፡፡
    ያ እንግዲህ ያ ነበር፡፡ባለፈው ሳምንት በቤንጋዚ ሊቢያ ውስጥ በሴፕቴምበር 11 የ አራት አሜሪካውያንን ሕይወት የቀጠፈውን በአሜሪካን ኮንሱሌት የደረሰውን ፍንዳታ አስመልክቶ ራይስ በሰጠችው ዘገባ የተነሳ የሪፓብሊካን ሴኔተሮች ጆን ማኬይንና ሊንድሲ ግራሃም ሱዛን ራይስን ጅል ደደብ ስራዋን የማታዉቅ ናት የሚል ሃያል አስተያየታቸውን ሰንዝረውባታል፡፡ ራይስ ከፍንዳታው አምስት ቀናት በኋላ በአምስት የተሌቪዝን ዜና ፕሮግራሞች ላይ ቀርባ፤ “በኮንስሌቱ ላይ የደረሰው ፍንዳታ ግብታዊ፤ በእቅድ ያልተደረገ፤ ነው:: በካይሮ በተነሳሳው ተቃውሞ ላይ የተመሰረተና ዋናው አነሳሽም አጸያፊውና አሳዛኝ የሆነው የእስላምን እምነት የሚያንቁያሽሽ የቪዲዮ ዝግጅት ያስከተለው ነው” በማለት ገለጠች፡፡ እንደ ራይስ አባባል፤በጥቂት ሰዎች ስብስብ ወደ ኤምባሲው የሄደው የተቃውሞ ትዕይንት በድንገት በተጠናከረ መሳርያ በታጠቁ አክራሪ ስብስቦች ‹‹ተጠልፎ›› ነው አደጋው የተፈጸመው ብላ ነበር፡፡

    The Tall Tale of Susan Rice


    by Alemayehu G. Mariam
    On September 2, 2012, Susan Rice, the U.S. Ambassador to the U.N., delivered a nauseatingly sentimental oration at the
    Susan Rice, the U.S. Ambassador to the U.N., Addis Ababa speech
     funeral of Ethiopian dictator Meles Zenawi. She called Meles “selfless and tireless” and “totally dedicated to his work and family.” She said he was “tough, unsentimental and sometimes unyielding. And, of course, he had little patience for fools, or idiots, as he liked to call them.”  The “fools” and “idiots” that Rice caricatured with rhetorical gusto and flair are Ethiopia’s  independent  journalists, opposition leaders, dissidents, political prisoners, civil society leaders and human rights advocates.Watching the video of her eulogy, one could easily say she “had gone native” completely. But it was clear that her aim was to deliver the last punch to the gut of Meles’ opponents as a sendoff present.

    As the old saying goes, “birds of a feather flock together”. Rice, like Meles, likes to insult and humiliate those who disagree with her. She had a reputation in the State Department as boor and a bit of a bully; or as those who knew her say, she was a “bull-in-a-china-shop”. She is known for verbal pyrotechnics, shouting matches and finger wagging at meetings. On one occasion, she is reported to have flipped her middle finger at the late Richard Holbrooke, the dean of American diplomats, at a senior State Department staff meeting. Prior to the onset of the air campaign in Libya in March 2012, France’s U.N. ambassador, Gerard Araud, advised Rice that the European Union would seek a no-fly zone resolution from the Security Council regardless of U.S. support. She gave Araud the verbal equivalent of a kick in the rear end: “You’re not going to drag us into your shitty war.” She later tried to claim full credit for the effort: “We need to be prepared to contemplate steps that include, but perhaps go beyond, a no-fly zone at this point, as the situation on the ground has evolved, and as a no-fly zone has inherent limitations in terms of protection of civilians at immediate risk.” This past July when China and Russia at the U.N. blocked adoption of language linking climate change to international security, she lambasted them as “pathetic” and “shortsighted” and accused them of “dereliction of duty.”
    That was then. In the past several days, Rice was on the receiving end. Republican Senators John McCain and Lindsey Graham virtually called Rice a fool and an idiot for her statements following the U.S. Consulate attack in Benghazi, Libya on September 11 in which four Americans were murdered. Rice appeared on five national Sunday talk shows five days after the attack and made the boldfaced claim that the attack on the consulate “was a spontaneous — not a premeditated — response to what had transpired in Cairo in response to this very offensive video that was disseminated”. According to Rice, the protest by a “small number of people who came to the consulate” was “hijacked” by “clusters of extremists who came with heavier weapons.”
    Senator McCain showed “little patience for fools, or idiots” and fairy tales when he angrily threatened  to block Rice if she were nominated to become Secretary of State: “Susan Rice should have known better, and if she didn’t know better, she’s not qualified. She has proven that she either doesn’t understand or she is not willing to accept evidence on its face. There is no doubt five days later what this attack was and for.”  Rice’s Benghazi story was reminiscent of the bedtime stories of the late Meles Zenawi.
    Truth be told, only a “fool” or an “idiot” would not know or reasonably surmise the attack on the U.S. consulate  was a terrorist act. CIA Director David Petraeus recently testified that from the moment he heard of the attack, he knew it was a terrorist act. He included this fact in the talking points he sent to the White House which somehow got redacted form Rice’s public statements. The experts and pundits also called it a terrorist act. For Rice, it was a protest gone wrong.
    But there remain a number of puzzling questions: Why was Rice selected to become the point person on the attack in light of President Obama’s defense that Rice “had nothing to do with Benghazi.” Why didn’t Hilary Clinton step up to explain what happened? Did the White House throw Rice under the bus to save Hilary? Was Rice supposed to provide plausible deniability and political cover until the election was over by calling a manifest terrorist attack a protest over an offensive anti-Muslim video?  Did Rice have to fall on the Benghazi sword to divert attention or delay accountability for the Administration’s failure to take appropriate preventive action in Benghazi as the price for nomination to the job of Secretary of State? Or was the White House trying to showcase Rice’s diplomatic adroitness and savvy in a futile attempt to bridge her unbridgeable competence and “stature gap” to become America’s foreign policy chief?
    President Obama was ready to drive a lance through the heart of Republican villains hell bent on capturing and devouring his prevaricating damsel in distress. He told McCain and Graham to bring it on. If the Republican duo and their buddies “want to go after somebody, they should go after me. But for them to go after the U.N. ambassador? Who had nothing to do with Benghazi? And was simply making a presentation based on intelligence that she had received? To besmirch her reputation is outrageous.” That was great drama staged by “no drama Obama.”

    Ethiopia’s ruling minority junta decides to remove the iconic statue of Martyred bishop, Abune Petros


    The Horn Times breaking News- November 23, 2012,
    by Getahune Bekele
    Ethiopian officials to remove the iconic statue of Martyred bishop, Abune Petros.
    “My countrymen… do not believe the fascists if they tell you that the patriots are bandits. The patriots are people who yearn for freedom from the terrors of fascism.
    “Bandits are the solders (Italians) who are standing in front of you and me; who came from afar to terrorize and violently occupy a weak but peaceful country. May God give the people of Ethiopia the strength to resist. Never to bow down to the fascist army and its violence.
    “May the Ethiopian soil never accept the invading army’s rule.”
    The last pithy words of his holiness Abune Petros, executed by the Italians on 29 July1936, for denouncing colonialism and brutal oppression.
    No one thought that the little shepherd born in the tiny northern town of Fiche would become a shining comet of Ethiopian patriotism which still flows from one generation to the other like the mighty river of Abaye.
    In the year 2000, honered as one of the millenniums’ martyrs by the church of Sweden, Abune Petros was just a young monk when fascist Italy invaded Ethiopia in 1932. That same year, the patriotic clergy followed emperor Hailesilassie to the decisive battle of Maichew where he witnessed the undiscerning terror of the invading Italian army.
    He watched Italian bombers spraying nerve gas, wiping out forests, burning villages and indiscriminately killing civilians.
    Later, he safely returned to the famous Debre Libanos monastery and started preaching against the invasion and unlawful occupation of Ethiopia, at times visiting the patriots and guerilla groups in their hideouts of central and northern highlands.
    However, in July 1936, he was captured inside Addis Ababa while encouraging the people to show merciless resistance to the Italians.
    Once in jail, the occupiers gave him an ultimatum of accepting the Italians as legitimate rulers or face death by hanging, to which he famously replied “the cry of my country men who were killed by nerve gas will never allow my conscious to accept your ultimatum. How can I see my God if I turn a blind eye to such a crime.”
    Soon after giving that incandescent speech, a swarm of bullets from the execution platoon killed the beloved bishop on July 29, 1936 in central Addis Ababa.
    His statue was raised 10 years after his death, a few meters away from where he was martyred.
    Nonetheless, according to fresh reports emerging out of Addis Ababa, the imposing structure will be demolished in the coming days to make way for a rail project that passes through the capital,  and it remains to be seen if such cruel move doesn’t incite the people of Ethiopia to open rebellion.
    As the junta continues to destroy the country’s revered heritage sites, the removal of Abune Petros’s statue will go down in history as the most ignoble and gruesome one.
    infohorntimes@gmail.com

    ላፍቶን አደራ


    ለወትሮዉ እንኳን ልቅሶና ኡኡታ ሹክ የሚል ድምጽም ደጋጋግሞ የማይሰማባት ላፍቶ በህፃናት፤በሴቶችና በአረጋዉያን የሰቆቃ ጩኸት እየተተራመሰች ነዉ። እናት የመንፈቅ ልጇን ታቅፋ እንዳታጠባዉ እሷ እራሷ ምግብ ከቀመሰች ሁለት ቀኗ ነዉና ጡቷ ደርቋል፤ እንዳታስተኛዉ ቤቷን የወያኔ ቡልዶዘሮች እንዳልነበረ አድርገዉታል።  አባት ሁለት ልጆቹን ታቅፎ አዉላላ ሜዳ ላይ ተኝቷል፤ ልጆቹ ቢነቁ የሚጠይቁትን የዉቃልና ቀኑን ሙሉ ቢተኙ ደስ ይለዋል። እሱም ቢሆን አንኳን የሚበላ “የሚላስ የሚቀመስ” የለዉምና ያለዉ አማራጭ መተኛት ብቻ ነዉ። ምግብ ወይም ስራ ፍለጋ እንዳይሄድ የእሱም መኖሪያ ቤት በወያኔ ቡልዶዘሮች ስለተናደ ሁለት ልጆቹን ጥሎ ዬትም መሄድ አይችልም።  የአዲስ አበባ ዉርጭ ሲነጋጋ ያንገበግባል፤ ቀን የፀሐዩ ሙቀት አታምጣ ነዉ፤  ሲመሽ ደግሞ ብርዱ ዛር እንደያዘዉ ሰዉ ያንቀጠቅጣል። ላፍቶ ዉስጥ ልብስ የለም፤ምግብ የለም መጠለያም የለም። እመጫት የመንፈቅ ልጇንና ባዶ ሆዷን ታቅፋ አባት ደግሞ ሁለት ልጆቹን ግራና ቀኝ አስተኝቶ ሁሉም  ጧት በዉርጭ፤ ቀን በሀሩር ማታ ደግሞ በብርድ ይጠበሳሉ። ይሄ ሁሉ የፍጥረት ሰቆቃ የሚታየዉ አዲስ አበባ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ዉስጥ ነዉ። ላፍቶን የመንግስት ጭካኔ፤ የከንቲባዋ ዝምታና የኗሪዎቿ  ጨኸት እረፍት ነስቷታል።  አዎ! ላፍቶ በአንድ በኩል በቡልዶዘር ጩኸት፤በሚፈርስ ቤት ጩኸትና ህዝቡን በሚያሸብሩ የፌዴራል ፖሊሶች ጩኸት በሌላ በኩል ደግሞ በህፃናት ልቅሶ፤ በአባቶች ኡኡታና በሴቶችና በአረጋዉያን ጩኸት ተወጥራለች። በንጉስ ሄሮድስ ዘመን “ጩኽት በራማ ተሰማ” ተብሎ በቅዱስ መጽሐፍ ዉስጥ እንደተጻፈ ዛሬም በወያኔ ዘመን ጩኸት በላፍቶ ተሰማ።
    ብዙ ህዝብ የሚኖርባት ላፍቶ በወያኔ ዘመን ከተስፋፉት የአዲስ አበባ ክፍለ ከተማዎች አንዷ ናት። እንደማንኛዉም የአዲስ አበባ ክፍለ ከተማ ላፍቶም ደሀዉ ጎጆዉ ቀልሶ ሀብታም ቪላ ገንብቶ ጎን ለጎን እየተያዩ የሚኖርባት ቦታ ናት። አቅም ካለዉ ላይና ታች አለዚያም  እንደአቅምቲ ዛኒጋባዉን ተክሎ የሚኖረዉ የላፍቶ ነዋሪና በፌዴራል ፖሊስ ቪላዉ የሚጠበቅለት የቦሌ ነዋሪ ሁለቱም እኩል ኢትዮጵያዉያን ናቸዉ። ፌዴራል ፖሊስ ዘራፊዎቹን የወያኔ ሹማምንት እቤታቸዉ ድረስ አጅቦ እያስገባ የላፍቶዉን ደሃ ደግሞ ቤቱን የሚያፈርስበት ምንም ምክንያት የለም። የከተማ ፕላን ወጥቶ ከተማ የሚገነባዉ ለህዝብ ህንጻዎች የሚሰሩትም ሆነ የሚፈርሱት ለህትዝብ ትቅም ሲባል ብቻ ነዉ። ኢትዮጵያ ዉስጥ ብቻ ሳይሆን ዬትም አገር ዉስጥ የህዝብን ጥቅምና ፍላጎት የሚጻረር ምንም ነገር አይሰራም ወይም አይፈርስም። ይህ በብዙ አገሮች ዉስጥ የሚሰራ ህግ ወያኔ በሚመራት ኢትዮጵያ ወስጥ አይሰራም። ኢትዮጵያ ዉስጥ የህዝብ ጥቅም ቢነካ ባይነካ የወያኔ ባልስልጣኖችና ጓደኞቻቸዉ አይን ያረፈበት ቤት ወይም ህንፃ ሰበብ ተፈልጎለት ይፈርሳል። የወያኔ ካድሬና ሹም ካልፈለገዉ በከፍተኛ ወጪ የተሰራ መንገድ ይፈርሳል ወይም መሰራት የሌለበት መንገድ ይሰራል።
    በቅርቡ የወያኔ ግፈኞች አላግባብ ቤት ሰርታችኋል ብለዉ ቤታቸዉን የፈረሱባቸዉ አባ ወራዎች ብዛት ለ17 ሺ ባላይ ነዉ፤ ይህ ቁጥር ደግሞ አባ ወራዎቹን ብቻ አንጂ እናቶችን፤ህጻናትንና የቅርብ ቤተሰብ አባላትን አያጠቃልልም። በፊዉዳሉ ስርአት ዉስጥ የመሬት ከበርቴዉ የጭሰኛዉን ጎጆ አፍርሶ የራሱን ይዞታ እንደሚያስፋፋ ሁሉ ዛሬም ወያኔ የከተሜዉን ቤት እያፈረሰ ቦታዉን የኔ ለሚላቸዉ ስግብግቦችና ለሆዳችዩ ላደሩ ምስለኔዎች እየሰጠ ነዉ። ወያኔ እንደለመደዉ ቤቱ የተሰራዉ ከህግ ዉጭ ነዉ እያለ ቢዋሽም በታቸዉ የፈረሰባቸዉ ሰዎች አንደተናገሩት ቤታቸዉን የሰሩት መንግስት ፈቅዶ ነዉ ወይም ቤቶቹ ሲሰሩና ተሰርተዉ አልቀዉ ቅዶ ነዉ ወይም ቤቶቹ ሲሰሩና ተሰርተዉ አልቀዉ ነዋሪዎቹ ሲገቡ ነዋሪዎቹ ሲገቡ ወያኔ ያዉቅ ነበር።  ባያዉቅስ? መንግስት ደፈርከኝ ብሎ ህዝብን የሚበቀል አካል አይደለም። የ60 ሺ ዜጎችን መኖሪያ ቤት አፍርሶ ነዋሪዎቹን ሜዳ ላይ የሚበትን መንግስት እንኳን ኢትዮጵያ ዉስጥ በአለማችንም የታየዉ በአፓርታይድ ደቡብ አፋሪካና በቀድሞዋ ሮዴሺያ ዉስጥ ብቻ ነዉ። እነዚህ ሁለት አገሮች ደግሞ ዘረኝነት የነገሰባቸዉ አገሮች ነበሩ። ይህንን ያክል ህዝብ ለአገር ጥቅም ሲባል መፍረስ ካለበት በመጀመሪያ ዜጎቹ የሚኖሩበት ቦታ ተፈልጎ መገኘት አለበት እንጂ የሰዉ ልጅ እንደለማዳ እንስሳ ከመኖሪያ ቤቱ ተገፍቶ ወጥቶ አይኑ እያየ መኖሪያ ቤቱ በቡሉዶዘር አይናድም። ለማዳ እንስሳ እንኳን ሌላ ቤት ይሰራለታል እንጂ ባዶ ሜዳ ላይ አይጣልም። ወያኔ ዘረኛ ነዉ የሚባለዉ ለካስ እንደዚህ የኔ አይደሉም የሚላቸዉን ዜጎች ከእንስሳ አሳንሶ ስለሚያይ ነዉ።
    ወያኔ ስሙ በተነሳ ቁጥር የሚዘገንነን ጭካኔዉ ብቻ አይደለም። ምንም አይነት የህዝብ ስሜት የማይገባዉና ለሀዝብ የሚያዝን ልብ የሌለዉ የደነዞች ስብስብ መሆኑ ነዉ።  በቅርቡ ላፍቶ ዉስጥ ፖሊስ ወላጆቻቸዉ ፊት በዱላ ቀጥቅጦ የገደላቸዉ የሁለት ህጻናት አሳዛኝ ሞት የሚያሳየን ይህንኑ የወያኔ ጭካኔና ለአገርና ለህዝብ የሚያሳየዉን ግድየለሽነት ነዉ። ለወትሮዉ “በአቡዬ” ና “በማሪያም” ስም የሚማጸነዉ የላፍቶ ህዝብ እነዚህ ደነዞች ቢገባቸዉ ብሎ የዚያን የደሃ አባት ተብሎ የተነገረለትን መሪ ፎቶ በደረቱ ታቅፎ ነበር የለመናቸዉ፤ ችግሩ የቤታቸዉ መፍረስና የእነሱና የልጆቻቸዉ መንገላታት የዚሁ ፎቶዉን የተሸከሙት ሰዉ ራዕይ ስለሆነ የሚሰማቸዉ ጠፋ።

    በሙስሊም ኢትዮጵያውያን ላይ የሚደርሰው ሰቆቃ እየጨመረ ነው ተባለ


    መንግስት ሙስሊሙ ላነሳው ጥያቄ ተገቢውንና ሰላማዊ የሆነ መፍትሄ ከመስጠት ይልቅ የሀይል አማራጭ መጠቀሙ፣ በሙስሊሙ ላይ የሚደርሰው በደል እየከፋ እንዲሄድ አድርጎታል።
    የአካባቢው ነዋሪዋች እንደተናገሩት  ካለፈው ሳምንት ጀምሮ በአማራ ክልል የኦሮሚያ ዞን ዋና ከተማ በሆነችው ከምሴ የፌደራል ፖሊስ አባላት ቤት ለቤት በመግባት ከ60 በላይ ሙስሊም ኢትዮጵያውያንን በመያዝ አስረዋል።
    በተያዙት ወጣቶች ላይ የሚደርሰው እንግልት እየጨመረ መምጣቱን ተከትሎ በርካታ ወጣቶች ቀያቸውን ለቀው ወደ ጂቡቲና ሱዳን ተሰደዋል።
    ከደጋንና ከሀርቡ አካባቢዎች ተነስተው ሱዳን ድንበርን እያቋረጡ የነበሩ ሙስሊሞች ለኢሳት በመደወል “    እኛ በአገራችን በነጻነት መኖር ስላልቻልን በመንገድ ስንጓዝ ጅብ ይብላን ብለን ጥለን እየሄድን ነው። የሱዳንንና የኢትዮጵያን ድንበር እያቋረጥን ነው፣ እንግዲህ አገራችንን አደራ፣ ሱዳን በሰላም ከገባን ድምጻችንን ታሰሙልናላችሁ፣ ያለበለዚያ ግን መንገድ ላይ ከተያዝን እንደማስረጃ አድርገው ስለሚያቀርቡብን መልእክታችንን ብቻ አቅርቡልን ” በማለት ተናግረዋል።
    በተመሳሳይ በትናንትናው እለት  በኢሊባቦር ዞን በመቱ ከተማ ከ400 በላይ ሙስሊሞች  የተቃውሞ ድምጽ ማሰማታቸውን ተከትሎ እስከ ምሽቱ 10 ሰአት ታግተው ውለዋል።
    የተወሰኑ ሙስሊሞችን ለማሰር ሙከራ ተደርጎ የነበረ ቢሆንም ፣ ህዝቡ ባሰማው ተቃውሞ ወዲያውኑ ሊፈቱ ችለዋል።
    የአሜሪካን መንግስት ጨምሮ የተለያዩ አለማቀፍ ድርጅቶች መንግስት የሙስሊሞችን ጥያቄ ለመፍታት እየተከተለ ያለው መንገድ ለኢትዮጵያ ህልውና አደጋ ይፈጥራል በማለት እያስጠነቀቀ ነው።